Tuesday, October 22, 2013

የእግዚአብሔርን አሳብ ማገልገል


                             ማክሰኞ ጥቅምት 12/2006 የምሕረት ዓመት

‹‹ . . . ዳዊትም በራሱ ዘመን የእግዚአብሔርን አሳብ ካገለገለ በኋላ አንቀላፋ፣ ከአባቶቹም ጋር ተጨምሮ መበስበስን አየ፤ ይህ እግዚአብሔር ያሥነሣው ግን መበስበስን አላየም›› (የሐዋ. 13፥36-39)

       ወዳጆች ሆይ ከሁሉ አስቀድሞ የጌታችንና የአምላካችን የመደኃኒታችንም የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ፡፡ በዚህ የጽሑፍ አገልግሎት የእግዚአብሔርን አሳብ ማገልገል ማለት ምን እንደ ሆነ የእግዚአብሔርን ቃል መሠረት በማድረግ እንካፈላለን፡፡ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ጸሐፊ በዚህ ክፍል ላይ ሁለት አገልጋዮችን በንጽጽር ያሳየናል፡፡ ይኸውም ነቢዩ ዳዊትንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ነው፡፡ ስለ ዳዊት የእግዚአብሔርን አሳብ አገልግሎ መበስበስን እንዳየ ሲፃፍ፤ ስለ ክርስቶስ ደግሞ የእግዚአብሔርን አሳብ አገልግሎ መበስበስን እንዳላየ ያስረዳናል፡፡ በዚህ ክፍል የእግዚአብሔርን አሳብ ማገልገል ምን እንደ ሆነ እንመልከት፡፡ ከዚያ በፊት ግን ጥቂት ጥያቄዎችን ለመንደርደሪያ እናንሣ፡፡

አገልግሎት ምንድነው?
የእግዚአብሔር አሳብስ ምን ማለት ነው?
የሚያገለግለው ማን ነው?
ሁሉ ሰው አገልጋይ ነውን?

Saturday, October 19, 2013

ከሻ . . . መልስ

                   

                          
                                ቅዳሜ ጥቅምት 9/ 2006 የምሕረት ዓመት

Saturday, October 12, 2013

Thursday, October 3, 2013

የስንኝ ገበታ 2


        ሐሙስ መስከረም 23/ 2006 የምሕረት ዓመት
 
ሕይወት እንቆቅልሽ ሕይወት አድር ባይ ናት፣
ኢየሱስ በደሙ ጨብጦ ካልያዛት፡፡
ሕሊና ተራቁቶ ማስመሰል ተላብሰን፣
እንዳንክድህ ጌታ ጸጋህ ይጠብቀን፡፡

የሄደ ላይመጣ ላለም ላይቀር መሄድ፣
 ሰው ሰውን ረግጦ አለፈው በመንገድ፣
 ልቤ እጄን ታዘበው ጨብጦ እንዳልሰጠ፣
 አካፍሎ የበላ ሰብስቦ ከራበው እጅጉን በለጠ፡፡