Friday, October 2, 2015

‹‹የመጽናናት ሁሉ አምላክ››


      (2 ቆሮ. 1፡3)
 
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አርብ መስከረም 21 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

          በቅዱሱ መጽሐፋችን ‹‹አጽናኑ፤ ሕዝቤን አጽናኑ፡ ይላል አምላካችሁ፡፡›› /ኢሳ. ፡1/ ተብሎ እንደተጻፈ፤ ክርስቲያኖች በፈተናና በመከራቸው እርስ በእርስ የሚጽናኑበት ‹‹የርኅራኄ አባትና የመጽናናት ሁሉ አምላክ›› እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ 
          እርሱ አምላካችን የዘላለም አምላክ፤ የምድር ዳርቻ ፈጣሪ፤ የማይደክም የማይታክት፤ ማስተዋሉም የማይመረመር፤ ሰማያትን የፈጠረ የዘረጋቸው፤ ምድርንና በውስጥዋ ያለውን ያጸና፤ በእርስዋ ላይ ለሚኖሩ ሕዝብ እስትንፋስን፣ ለሚሄዱባትም መንፈስን የሚሰጥ ነው፡፡