Friday, April 29, 2016

አፋችሁን አትክፈቱ!

    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


                 

              ‹‹ኢከሰተ አፉሁ በሕማሙ›› እንዲል (ሐዋ. 832)::

  አርብ ሚያዚያ 21 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

          የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ሁለተኛው ክፍል ‹‹የታሪክ ክፍል›› በመባል ይታወቃል፡፡ ይህም ከአገልጋዮቹ አንጻር ‹‹የሐዋርያት ሥራ››፤ ከሥራው ባለቤት አንጻር ደግሞ ‹‹የመንፈስ ቅዱስ ሥራ›› በመባል የሚታወቀው መጽሐፍ ነው፡፡ ‹‹ለድፍርስ መፍትሔው ምንጭ መውረድ ነው›› የማወቅ መመሪያዬ ነው፡፡ የክርስትናን መሠረተ ጅማሬ ለሥጋና ደም አሳብ ክፍተት በማይሰጥ መልኩ ቁልጭ ብሎ በምንመለከትበት በዚህ መጽሐፍ ውስጥ፤ በሞተውና ከሙታንም በተነሣው በክርስቶስ ክርስቲያን የሆኑቱ በኅብረት የተቀበሉትን (ቤተ፡ ክርስቲያን) የመጀመሪያውን ታላቅ መከራና ስደት እናነባለን፤ ከእስጢፋኖስ መገደል በኋላ (ከሐዋርያት ሥራ ም. 7)፡፡


     ምእራፍ ስምንት ስደትና መከራውን (ክርስቶስ ስለ ጽድቅ የተቀበለውን መከራ መካፈል) ተከትሎ ወደ ይሁዳና ወደ ሰማርያ የሆነውን መበተን መርዶ በመንገር ይጀምራል፡፡ ይህንን ምእራፍ እንዲህ ከፍለን ልንረዳው እንችላለን፡ - 

                  1. በክርስትና የመጀመሪያው ታላቅ መከራ (ከቁ. 1-3)
                  2. የተበተኑት ምእመናን ወንጌልን መስበካቸውና ፊልጶስ በሰማርያ (4-8)
                  3. የሰማርያው ጠንቋይ ሲሞን እና በዚያ የሆነው (9-24)
                  4. ወንጌል በሳምራውያን ብዙ መንደሮች መሰበኩ (ቁ. 25)
                  5. ፊልጶስና ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ (26-40)

መልእክት ፡ ኀበ ፡ ሰብአ ፡ ኤፌሶን፡፡ (1)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


የሐዋርያው ፡ የጳውሎስ ፡ መልእክት ፡ ወደ ፡ ኤፌሶን ፡ ሰዎች፡፡

አርብ ሚያዚያ 21 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

    ‹‹ወአርአየነ ምክረ ፈቃዱ በከመ ሥምረቱ›› (ኤፌ. 1፡9)!

·        የመልእክቱ ጸሐፊ፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
መልእክቱ የተጻፈበት ጊዜ፡ ከ61-63 ዓ/ም ባሉት ዓመታት
·        መልእክቱ የተጻፈበት ቦታ፡ ሮም
በጊዜው የመልእክቱ ተቀባዮች፡ የኤፌሶን ቤተ፡ ክርስቲያን (ማኅበረ ምእመናን)
·        የመልእክቱ ጭብጥ፡ የክርስቶስ ባለ ጠግነት በቤተ፡ ክርስቲያን 
(The Orthodox study Bible) 

Saturday, April 9, 2016

መልእክት ኀበ ፊልሞና፡፡ (8)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! 


ቅዳሜ ሚያዚያ 1 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

(መልእክት ወደ ፊልሞና)

‹‹እምጳውሎስ ሙቁሐ ለኢየሱስ ክርስቶስ፡ (ኤፌ. 3፡1)!››

No. 14-17, ‹‹While the master-slave relationship continues, it is transcended by brotherhood in Christ.›› /The Orthodox Study Bible; New Testament and Psalms New King James Version/.

‹‹አምኀከ ኤጳፍራስ ዘተጼወወ ምስሌየ በኢየሱስ ክርስቶስ፡፡››
‹‹በክርስቶስ ኢየሱስ ከእኔ ጋር የታሰረ ኤጳፍራ . . ››፡-

          ሐዋርያው ጳውሎስ በዚህ መልእክት የስንብት ክፍል የጠቀሰው ሌላው የተወደደ አገልጋይ ኤጳፍራ ነው፡፡ ሐዋርያው ይህንን መልእክት የጻፈው በእስር ቤት ሆኖ እንደ መሆኑ፤ አብሮት ስለ ክርስቶስ የታሠረ ሌላውን አገልጋይ ይጠቅሳል፡፡ ባለፈው ጥናታችን ሐዋርያው ከእስር ተፈትቶ በፊልሞና ቤት ያለችውን ቤተ ክርስቲያን እንደሚጎበኛት ያለውን ተስፋ ለተወደደውና አብሮት ለሚሠራ ለፊልሞና ሲገልጽለት አይተናል፡፡

        በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ስለ ኤጳፍራ የምናገኘውን ምስክርነት በመመልከት የእግዚአብሔር መንፈስ የሚያስተምረንን እንወስዳለን፡፡ በቆላስይስ መልእክት ‹‹ከተወደደ ከእኛም ጋር አብሮ ባሪያ ከሆነው ከኤጳፍራ እንዲህ ተማራችሁ፤ እርሱም ስለ እናንተ ታማኝ የክርስቶስ አገልጋይ ነው፡፡ ደግሞም በመንፈስ ስለሚሆን ስለ ፍቅራችሁ አስታወቀን፡፡›› (ቆላ. 1፡7-8) የሚል ምስክርነት በሐዋርያው ተጽፎ እናነባለን፡፡   

Friday, April 8, 2016

መልእክት ኀበ ፊልሞና፡፡(7)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


አርብ መጋቢት 30 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

(መልእክት ወደ ፊልሞና)

‹‹እምጳውሎስ ሙቁሐ ለኢየሱስ ክርስቶስ፡ (ኤፌ. 3፡1)!››

‹‹አእሚርየ ከመ ትወስክ እንዘ አዘዝኩከ፤ ካዘዝሁህም አብልጠህ እንድትሠራ ዐውቄ ጻፍኩልህ፡፡›› /ቁ. 21/

         ፍቅርን ለሚመለከቱ ቅን ልቦች የፊልሞና መልእክት መዋደድን ሊሞላን የሚችል ቅዱስ አሳብ የያዘ መጽሐፍ ነው፡፡ ግንኙነቶቻችንን የምንጠብቅበት ሰማያዊ መመሪያና መለኮታዊ አካሄድን በጥልቀት እንረዳበታለን፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በፊልሞና እና በአናሲሞስ መካከል የተፈጠረውን መለያየት አስመልክቶ ‹‹ልቡን  የሚያሳርፍ›› መፍትሔ እንዲመጣ በፍቅር ዝቅ ማለቱን እንመለከታለን፡፡ በአገራችን የሰዎችን አለመግባባት ለመፍታት የሚያስተራርቁ ሰዎች ድንጋይ ጭምር ተሸክመው በመካከል እንደሚቆሙ እናውቃለን፡፡

        በዚህ አጭር መልእክት ውስጥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሥር ጊዜ ተጠቅሷል፡፡ ኢዮብ ‹‹ይኸው ስትሰድቡኝ አሥር ጊዜ ነው፤ ስታሻክሩኝም አላፈራችሁም›› (ኢዮ. 19፡3) እንዳለ፤ እንዲሁም በልማድ ‹‹አሥር ጊዜ አትነዝንዘኝ›› እንደሚባል (ይህንን ለመጀመሪያ ጊዜ ያለው የመጽሐፉ ኢዮብ ይመስለኛል)፤ ሐዋርያው ለቆሮንቆስ ምእመናን ‹‹ነገር ግን ወንድሞች ሆይ፤ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ›› (1 ቆሮ. 1፡10) ያለውን እዚህም ተግባራዊ እንዳደረገ ልናስብ እንችላለን፡፡     

Saturday, April 2, 2016

መጻጉዕ፡ የባሰ አለ


ቅዳሜ መጋቢት 24 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

‹‹ . . እንዴት ይልቅ የሚብስ ቅጣት የሚገባው ይመስላችኋል?›› /ዕብ. 10፡28/!