በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ሐሙስ መስከረም 6 ቀን 2009 የጸጋ ዓመት
መጽሐፍ ‹‹በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ›› (ሮሜ 3፡24) ሲል፤ ክርስቲያን የጽድቅን ሥራ አይሠራም ማለት አይደለም፡፡ የጸደቀ ዛፍ ያለ ፍሬ ሊሆን እንደማይችል፤ ከሥሩ በግንዱ በኩል ቅርንጫፎች እየተመገቡ ያፈራሉ፡፡
‹‹ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና›› (ሮሜ 1፡17) ተብሎ እንደተጻፈ፤ በእምነትና በጽድቅ ሥራ እያደግን፤ እርሱ ጽድቃችን ጌታ ኃጢአትን እንደሚጠላ ከበደል እየራቅን የምንኖር እንሆናለን፡፡ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ደኅንነትን ያገኙና ጽድቅ የሆነላቸው ሁሉ ኃጢአትን ባለማድረግ መርኅ ውስጥ እየኖሩ (1 ዮሐ. 2፡1)፤ በሚሆነው ድካማቸው በዳኑበት በዚያው ደም በንስሐ ይታጠባሉ (1 ዮሐ. 1፡7)፡፡


