በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
‹‹ድልም ብዙ ምክር ባለበት ዘንድ ነው›› /ምሳ. 24፡6/፤ ‹‹እርስ በርሳችን እንመካከር›› /ዕብ. 10፡25/!
‹‹ድልም ብዙ ምክር ባለበት ዘንድ ነው›› /ምሳ. 24፡6/፤ ‹‹እርስ በርሳችን እንመካከር›› /ዕብ. 10፡25/!
ሐሙስ ታህሳስ 7 ቀን
2008 የምሕረት ዓመት
ፈተና
የምንኖርበት የአሁኑ ዓለም አንደኛው መልክ ነው፡፡ የኖረ ይቸገራል፤ የሚራመድን እንቅፋት ይመታዋል፡፡ መኖር ባይኖር መቸገር ከወዴት
አለ? መንቀሳቀስስ ባይኖር እንቅፋት ከወዴት አለ? በዓለም ሳለን መከራ እንዳለብን ይህ አስቀድሞ የተባለ አይደለምን? (ዮሐ.
16፡33)፡፡ ተወዳጆች ሆይ፤ ችግርን ብርቱ ዓይን ሲመለከተውና ደካማ ሲያየው የተለያየ ነው፤ ፈተና በሚያስተውል ሰው ጆሮና በማያስተውል
ዘንድ ሲሰማ ሁለቱም ጋር አንድ አይደለም፡፡
ለችግሮች ጊዜያዊ መፍትሔ ስለ መፈለግ ከምትደክሙ ራሳችሁን በጥንካሬ
መገንባት ላይ ጊዜ ውሰዱ፡፡ ፈተና በማንኛውም ጊዜ ሊመጣ ይችላል፡፡ ዳሩ ግን ዛሬ ያልተሠራ ማንነታችሁን በቅጽበት አልያም ውስን
በሆነ ጊዜ ውስጥ አትገነቡትም፤ ሁኔታዎችን ለመቀየር ከመድከም ራስን መቀየር ላይ ትኩረት ማድረግ ይበልጣል፡፡ በዚህም ችግር የማይጠጋው
ሰው ሳይሆን ችግርን በትክክለኛው መንገድ የሚፈታ ሰው ትሆናላችሁ፡፡





