Thursday, September 29, 2016

የተደረገልን /4/


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
 ሐሙስ መስከረም 19 ቀን 2009 የጸጋ ዓመት

‹‹ቤዛነት››


Monday, September 26, 2016

መልሱ ላይ ጥያቄ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


ሰኞ መስከረም 16 ቀን 2009 የጸጋ ዓመት

‹‹ፍቅርም እውነትም ማን ነው?››

       ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የመስቀል አደባባዩ ትልቁ ደመራ፤ ትንንሽ ደመራ ልጆች በየአካባቢው መታየታቸው እየተለመደ መጥቶአል፡፡ ይህ ሊሆን የቻለበትን ብንመረምር ደግሞ ብዙ ምክንያቶችን ልናገኝ እንችላለን፡፡ ነገር ግን ሁሉም ሰው በቀላሉ የሚያስተውለውን ለማየት ብንሞክር ሃይማኖታዊ መልክና ዓለማዊ መልክ ብለን በሁለት ልንከፍለው እንችላለን፡፡

      ከእምነት ጋር በተያያዘ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የመስቀሉን ቃል ይዞ ታሪካዊ የሆነውን ተዛምዶ በማስከተል በዓል የሚያደርጉትን ልብ ስንል፤ ከዚህ ውጪ የሆነው ደግሞ መጠጥ ማሻሻጫ፤ የሥጋን ጥያቄ በመንፈሳዊ ሽፋን ማርኪያ፤ ከአላፊ አግዳሚው ገንዘብ መሰብሰቢያ፤ መዝፈን መጨፈሪያ፤ ይህንንም የሚመስል ሁሉ ነው፡፡

      ለዚህ ጽሑፍ የመጻፍ ግፊት ኃይል የሆነኝ ዛሬ ማለዳ በተንቀሳቀስኩበት አካባቢ ዓይኖቼ የተመለከቱት ጽሑፍ ነው፡፡ ምሽት ሊለኮስ አንድ መጠት ቤት ፊት ለፊት የተደመረ ደመራ ጉልላት ላያ፤ የተመሳቀለውን እንጨትና ጉንጉን አበባ ታኮ በነጭ ወረቀት በጥቁር እስክርቢቶ የተጻፈ ‹‹ፍቅርም እውነትም ማን ነው?›› የሚል ትልቅ ጥያቄ ላይ ዓይኖቼ አረፉ፡፡ አሥር ደቂቃ ቆሜ ብዙ አሰብኩ፡፡ ነገር ግን ቀለል አድርጌ ላየው በሞከርኩ ቁጥር ዙር እየከረረ፤ ነገሩ እየከበደ መጣብኝ፡፡ እናም ውስጤ ‹‹መልሱ ላይ ጥያቄ›› የሚል ርዕስ ተፈጠረ፡፡

    ፍቅር እና እውነት በክርስትና ውስጥ እጅግ መሰረታዊ ነገሮች ናቸው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያው ጳውሎስ በኩል ‹‹ . . በተጠራችሁበት መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ›› ባለበት ክፍል ‹‹ . . እውነትን በፍቅር እየያዝን በነገር ሁሉ ወደ እርሱ ራስ ወደሚሆን ወደ ክርስቶስ እንደግ›› (ኤፌ. 4፡15) ይለናል፡፡ እውነት ያመንበት መሰረት ሲሆን፤ ፍቅር ደግሞ ያመነውን በተግባር የምንገልጥበት መንገድ ነው፡፡ እውነት ኖሯቸው ፍቅር የሌላቸው እውነቱን የብቻቸው ከማድረግ ጀምሮ ሌላውን ለመጉዳት ጭምር ሊያውሉት ይችላሉ፡፡ ፍቅር ኖሯቸው እውነቱ የሌላቸው ደግሞ ሚዛን በሌለው ፍቅር እውነትን እየረገጡ ይበድላሉ፡፡

Friday, September 16, 2016

የተደረገልን /3/


                በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 ሐሙስ መስከረም 6 ቀን 2009 የጸጋ ዓመት

       መጽሐፍ ‹‹በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ›› (ሮሜ 3፡24) ሲል፤ ክርስቲያን የጽድቅን ሥራ አይሠራም ማለት አይደለም፡፡ የጸደቀ ዛፍ ያለ ፍሬ ሊሆን እንደማይችል፤ ከሥሩ በግንዱ በኩል ቅርንጫፎች እየተመገቡ ያፈራሉ፡፡


      ‹‹ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና›› (ሮሜ 1፡17) ተብሎ እንደተጻፈ፤ በእምነትና በጽድቅ ሥራ እያደግን፤ እርሱ ጽድቃችን ጌታ ኃጢአትን እንደሚጠላ ከበደል እየራቅን የምንኖር እንሆናለን፡፡ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ደኅንነትን ያገኙና ጽድቅ የሆነላቸው ሁሉ ኃጢአትን ባለማድረግ መርኅ ውስጥ እየኖሩ (1 ዮሐ. 2፡1)፤ በሚሆነው ድካማቸው በዳኑበት በዚያው ደም በንስሐ ይታጠባሉ (1 ዮሐ. 1፡7)፡፡

Sunday, September 11, 2016

ከይሳኮር የሚበልጥ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን


እሑድ መስከረም 1 ቀን 2009 የጸጋ ዓመት
      ቀጣዩን (የሚሆነውን) የማወቅ ጉጉት በማንኛውም ሰው ውስጥ ያለ የጋራ ፍላጎት እንደ ሆነ ይስተዋላል፡፡ ምንም እንኳ ‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና፤ ለነገ አትጨነቁ፤ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል›› (ማቴ. 6፡34) ተብሎ በቅዱሱ መጽሐፋችን የተጻፈ ቢሆንም፤ ምድር ብርቱ ሠልፍ አላትና በክርስትናችንም እንዲህ የምናውቀውን ቃል መታዘዝ ጭንቅ ይሆናል፡፡ ደግሞ ቀጣዩ ምን ይሆን?፤ ኖሬ ምን ይገጥመኛል? የሚሉ ጥያቄዎች፤ ‹‹አይመጣምን ትተሽ ይመጣልን አስቢ›› አይነት አባባሎች . . ወዘተ፤ ሰው በቀጣዩ ላይ ያለው ሥጋት ከፍተኛ መሆኑን ያሳብቃሉ፡፡
      በመጽሐፍ ቅዱሳችን የመጀመሪያ ክፍል ‹‹ያዕቆብ ልጆቹን ጠርቶ እንዲህ አለ፡- በኋለኛው ዘመን የሚያገኛችሁን እንድነግራችሁ ተሰብሰቡ፡፡›› (ዘፍ. 49፡1-28) ተብሎ ተጽፎአል፡፡ የብዙዎች አባት አብርሃም፤ ሳቅ የሆነውን ይስሐቅን ወለደ፤ እርሱ ደግሞ አሰናካይ የሆነውን ያዕቆብን ወለደ፡፡ ያዕቆብ ከእርሱ ከራሱ በሆነው ብልጣ ብልጥነት ብዙ ዘመኑን የደከመ ቢሆንም በጎልማስነቱ ጊዜ ከአምላክ ጋር ታገለ፤ አልቅሶም ለመነው (ሆሴ. 11፡4)፡፡ እግዚአብሔር ያዕቆብን ስሙን ለእግዚአብሔር የሚዋጋ ሲል እስራኤል አለው፡፡ ያዕቆብ ከእግዚአብሔር ጋር ትክክለኛ ግንኙነት ወደ ማድረግ የመጣው ከስሙ መቀየር ጋር ተከትሎ ሆነ፡፡ ይህም በቀጣይ ኑሮው ላይ ግልጽ ለውጦችን አምጥቶአል፡፡

      መድኃኒታችን ኢየሱስ ለአገልግሎቱ ሾሞ፤ ታማኝ አድርጎ የቆጠረውን ሐዋርያ ጳውሎስ (1 ጢሞ. 1፡12) አስቀድሞ የነበረውን ስም በመቀየር (ሐዋ. 9)፤ ታናሽ የሚለውን የስም ፍቺ ይዞ ለጌታ ምርጥ ዕቃው ሆኗል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ስምን ከተግባራዊ ባህርይ ጋርም ያያይዘዋል፡፡ በእርግጥም ዙሪያችንን አጥርተን ብናይ ስም በባህርይ ላይ ያለውን ተጽእኖ በግልጽ ልናይ እንችላለን፡፡ ሰው ዘመኑን በብዛት የሚሰማው የራሱን ስም ነውና፡፡ ወላጆች ለልጆች የስም ስያሜ ሲያወጡ፤ ልጆችም በወጣላቸው ስያሜ ሲጠሩ ማስተዋልና ለዚያ መጠንቀቅ ተገቢ ይሆናል፡፡


Monday, September 5, 2016

‹‹መስሚያው ጥጥ››

 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


ሰኞ ነሐሴ 30 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

        ከበርሃማው የመልክዓ ምድር ክልል አንዱ፤ ከጥቂት መልካሞች እንደ እድለኛ  ያደኩበትን የድሮውን ሳስታውስ ከማረሳቸው ሰዎች መካከል የድጓ መምህር የኔታ ብርሃኑ አንዱ ነበሩ፡፡ ሰው ለእግዚአብሔር በማይታጭበት፤ በልዩ ልዩ ሱስ መጠመድ እንደ ነቄ በሚያስቆጥርበት፤ ለሕያው አምላክ ማድላት ፋራና ፈሪ በሚያሰኝበት መዝሙረ ዳዊት ሁለቴ ዘልቆ ማጠናቀቅ እንደ ብርቅ በሚታይበት ማኅበረሰብ፤ እንደተረዱት መጠን ለእግዚአብሔር አገልግሎት ወንዶችን ያቀርቡ ዘንድ የኔታ በትጋት ያስተምሩን ነበር፡፡

        አንድ ቀን የሰኞ መስተጋብ ላዜም በተለመደው ሰዓት ወደ መቃብር ቤታቸው ስሄድ፤ በበሩ ትይዩ ባለው ሽቦ አልጋቸው ላይ በቁጭ አቀርቅረው ትልቅ መጽሐፍ ያነባሉ፡፡ ወደ ውስጥ ለመዝለቅ ፈቃዳቸውን በሚጠይቅ ዜማዊ አነጋገር የኔታ . . የኔታ . . እያልኩ በተደጋጋሚ ከስተውጪ ወደ ውስጥ ገርበብ ባለው ብረት በር በኩል እጣራለሁ፡፡