Friday, September 26, 2014

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር፡


/ካለፈው የቀጠለ/
                  (መዝ. 123÷1-8)
                          መስከረም 16 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

        ከእናንተ ጋር ያላችሁ ምንድነው? መቼም አንድ ነገር እያለን፤ ነገር ግን እንዳለን ባናውቅ ይህ እጅግ ያሳዝናል፡፡ የፍቅር ሐዋርያው ዮሐንስ ‹‹የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ›› /1 ዮሐ. 5÷13/ ሲል፤ የዘላለም ሕይወትን የተቀበሉ ግን ደግሞ ይህንን የተሰጣቸውን ሕይወት ያላስተዋሉ ክርስቲያኖችን ልብ እንላለን፡፡ ተወዳጆች ሆይ፤ ይህንን አለመረዳት ትርጉሙ ቀላል አይሆንም፡፡ ኪሳራውም እጅግ የከፋ ነው፡፡

       የእግዚአብሔር ሰዎች ያላቸው ትልቁ ‹‹እግዚአብሔር›› ብቻ ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር አለመሆኑ ምን ሊያመጣ እንደሚችል በተረዳው መጠን ይናገራል፡፡ በዚህ መዝሙር ውስጥ ያሉትን አሳቦች በሁለት ከፍለን ልናያቸው እንችላለን፡፡ የመጀመሪያው ካለፈው ነገር ጋር የተያያዘ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ከመጪው ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ባለፈው ጊዜ ካለፈው ኑሮ ጋር የተያያዘውን አሳብ ማየት ጀምረን ነበር፡፡ በዚህም ክፍል አሳቦቹን በዝርዝር እናያለን፡፡

Thursday, September 11, 2014

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር፡

                 (መዝ. 123÷1-8)

                           መስከረም 1 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

     ስላልተሳኩልን ነገሮች ማስታወስ ለሰው እያደር የሚመረቅዝ ቁስል ነው፡፡ ምስጋናችንን ምሬት፤ እልልታችንን ጩኸት፤ ደስታችንን ዕንባ እየቀደመው የምንቸገርበትም ርዕስ ይህ ነው፡፡ ተወዳጆች ሆይ፤ ወደ ኋላ መለስ ብላችሁ ያለፈውን ስታስቡ ለልባችሁ የቀረው ነገር ምንድነው? ያጣችሁት ወይስ ያገኛችሁት? የተደረገላችሁ ወይስ የተወሰደባችሁ? ምሬት ወይስ ሐሴት? የትኛው ሚዛን ይደፋል? ‹‹ዘመን መለወጡ፤ በእድሜ መባረኩ፤ ተጨማሪ ዕድል ማግኘቱ ልባችንን በደስታ ያጠግባልን?›› ብለን እንደ ክርስቲያን ብንጠይቅ ጥያቄያችን ጥያቄን፤ ጥማታችን የበለጠ መጠማትን ያገናኘናል፡፡ ያለ እግዚአብሔር ሕልውና አለመኖር ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር አለመሆናቸውን ሲወቅሱ፤ እግዚአብሔር በዚያም ውስጥ ከእነርሱ ጋር በመሆኑ ግን አይደነቁም፡፡ የተዋችሁት ከያዛችሁ፤ ቸል ያላችሁት ካልረሳችሁ ከዚህ የሚበልጥ ምን የምስጋና ርዕስ አለ?

Wednesday, September 10, 2014

አንተ ግን፡

 ‹‹አንተ ግን፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ የምነግርህን ስማ እንደዚያ እንደ ዓመፀኛው ቤት ዓመፀኛ አትሁን አፍህን ክፈት የምሰጥህንም ብላ።››  /ሕዝ. 28/