Friday, December 25, 2015

መልእክት ኀበ ፊልሞና፡፡(2)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


አርብ ታኅሣሥ 15 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

(መልእክት ወደ ፊልሞና)

‹‹እምጳውሎስ ሙቁሐ ለኢየሱስ ክርስቶስ፡ (ኤፌ. 3፡1)››!

           መጽሐፍ ቅዱሳችሁን ከመክፈታችሁ፤ እንዲሁም የመልእክቱን ክፍል ከመግለጣችሁ አስቀድሞ አብ፤ ወልድ፤ መንፈስ ቅዱስ፤ አንድ አምላክ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ማስተዋልን እንዲሰጣችሁ፤ እንዲሁም ከመልእክቱ ልትረዱ የሚገባችሁን ሁሉ መቀበል እንድትችሉ በቅዱስ መንፈሱ በኩል እንዲረዳችሁ በመንፈስና በእውነት በመገዛት ጸልዩ፡፡ ተወዳጆች ሆይ፤ ከዚህ በኋላ መልእክቱን ቃል በቃል በጥንቃቄና በእርጋታ አንብቡት፤ ይህንንም በመደጋገም አድርጉት፡፡

የመልእክቱ ዳሰሳ፡-

o   ‹‹ተቀብለህ ለዘላለም እንድትይዘው . . ›› /ቁ. 15/ የመልእክቱ ዋና አሳብ ሲሆን፤ ለመልእክቱ ‹‹የዘላለም መያያዝ›› ብለን ርእስ ልንሰጠው እንችላለን፡፡ ሐዋርያው ለፊልሞና ‹‹እንደ ባልንጀራ ብትቆጥረኝ እንደ እኔ አድርገህ ተቀበለው›› /ቁ. 17/ በማለት ይጠይቃል፡፡

o   መልእክቱ ከሐዋርያው ከጳውሎስ መልእክታት በጣም አጭሩ መልእክት ሲሆን፤ ሐዋርያው በእስር ቤት ሆኖ ከጻፋቸው ከፊልጵስዩስ፤ ከቆላስይስ እና ከኤፌሶን መልእክታት መካከል አንዱ ሲሆን፤ ይዘቱ ግን የተለየ ነው፡፡


o   ሐዋርያው ከጻፋቸው መልእክታት መካከል ለሦስት ሰዎች (ግለሰቦች) የጻፋቸው አራት መልእክታት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህም፡- አንደኛ ጢሞቴዎስ፤ ሁለተኛ ጢሞቴዎስ፤ ቲቶ እና አሁን እያጠናነው ያለነው የፊልሞና መልእክት ናቸው፡፡ መልእክቱን ወደራሳችሁ አቅርባችሁ፤ ለእናንተ እንደተላከ በመቁጠር ብታነቡት በእጅጉ ትጠቀማላችሁ፡፡

o   በመልእክቱ አሳብ ውስጥ ቁልፍ የሆኑ (ትኩረት የሚሰጣቸው) ቃላትን እናገኛለን፡፡ እነዚህም፡- ክብር፤ ቸርነት፤ ጥንቃቄ፤ ወዳጅ፤ ፍቅር፤ ትህትና፤ ጥበብ፤ ግልጽ የሆነ ንጽህና (ቅድስና)፤ ከዚህ በመነሣት የመልእክቱን ይዘት ‹‹ትህትናን የተላበሰ መልእክት›› እንደሆነ እናስተውላለን፡፡ ተወዳጆች ሆይ፤ በዚህ መልእክት ውስጥ ችግር ፈቺ የሆነውን ክርስትና ለመመልከት ሞክሩ፡፡

o   መልእክቱ ባለ ሀብት የነበረው የቆላስይስ ክርስቲያን እና የሐዋርያው የጳውሎስ ቅርብ ወዳጅ የፊልሞና ባሪያ አናሲሞስ (ጠቃሚ፤ ዋጋ ያለው ማለት ነው) ከጌታው ወደ ሮም ኮብልሎ መጥፋቱ፤ በኋላም በክርስቶስ ክርስቲያን ሆኖ ወደ አሳዳሪው መመለሱን ማእከል ያደረገ ‹‹የእርቅ›› ደብዳቤ ነው፡፡ ተወዳጆች ሆይ፤ ጥሩ የማይባለውን አጋጣሚ ጌታ አንድን ነፍስ ወደ ክብር ለማምጣት እንዴት ለበጎ እንደ ተጠቀመበት አስተውሉ፡፡

o   መልእክቱ የ‹‹እርስ በርስ መዋደድን›› /ዮሐ. 13፡34/ አዲስ ትእዛዝ መሰረት ያደረገው የክርስትና ኑሮ የፍቅር ገጽታ ምን እንደሚመስል በተግባር የሚያስረዳ ሲሆን፤ በዓለም ላይ የሰዎች ባርነት (ስቃይን ጭምር የተሞላ) ተስፋፍቶ በነበረበት የሐዋርያት ዘመን ባሪያን አስመልክቶ የተጻፈ ብቸኛው መልእክት ነው፡፡ በዚህም ክርስትና የባርነትን ችግር ለመፍታት ያለውን የላቀ መንገድ የሚያሳይ ጽሑፍ ሆኖ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡

o   ሐዋርያው በቆላስይስ መልእክቱ ላይ ‹‹ከእናንተ ከሆነውና ከታመነው ከተወደደውም ወንድም ከአናሲሞስ . . ›› /ቆላ. 4፡9/ ብሎ እንደጻፈው፤ ፊልሞና በቆላስይስ የሚኖር ባሪያ አሳዳሪና ቤተክርስቲያኒቱም (የምእመናን ስብስብ) በቤቱ የነበረች እንደሆነ፤ እንዲሁም የፊልሞና መልእክት እና የቆላስይስ መልእክት በተመሳሳይ ጊዜ የተጻፉና የተላኩ መሆኑን እንረዳለን፡፡ በዚህ ክፍል መሰረት መልእክቱ የተላከው ‹‹በአናሲሞስና በቲኪቆስ›› እጅ ነው፡፡    

‹‹ጽኑዕ ኃያል ለምጻም››

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


አርብ ታኅሣሥ 15 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

        እግዚአብሔር የሌለበት ጀግንነት፤ እርሱ ሞገስ ያልሆነለት ከፍታ፤ ቅዱሱን አምላክ የማያሳይ መክበር፤ ለእርሱም የማይገዛ ሥልጣንና ባለ ጠግነት እጅግ ከንቱ ነው (ሉቃ. 12፡21)፡፡ ጌታችን ‹‹ከእኔ ጋርም የማያከማች ይበትናል።›› (ማቴ. 12፡30) ብሎ እንደተናገረ፤ ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም ማድረግ ከየትኛውም ብልጥግና የላቀ ነው (ኢሳ. 27፡5-6)፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል?›› /ማቴ. 16፡26/ እንዳለን፤ ለሰው ወደ እግዚአብሔር እንደመድረስ ያለ ስኬት፤ ብልጥግናም የለም፡፡

         የሶሪያ ንጉሥ ሠራዊት አለቃ ንዕማን፤ በጌታው (በንጉሡ) ዘንድ ታላቅ ክቡር ሰው ነበረ፤ ደግሞም ጽኑዕ ኃያል ነበረ (2 ነገ. 5፡1-4)፤ ነገር ግን ለምጻም ነበረ፡፡ የሠራዊት አለቃ ለምጻም፤ ታላቅ ክቡር ሰው ለምጻም፤ ጽኑ ኃያል ለምጻም ነበረ፡፡ ከአህዛብ የሆነውን ይህን ሰው ከእግዚአብሔር ቃል በቀር ማን እንዲህ ሊለው ይችል ነበር? ከስሩ የሚታዘዙ ሎሌዎቹ ታሪኩን ቢጽፉት ኖሮ እንዲህ ተጽፎ አናነብም፡፡ የአለቆቻቸውን ግብር እየበሉ ታሪክ አምታተው ስለጻፉ ተወቃሾች ብዙ የሚባልባት አገር ላይ እንዳለን አንስተውም፡፡ እግዚአብሔር ብቻ ልካችሁን ይናገራል፡፡

Thursday, December 17, 2015

ድልና ምክር (2)

                          በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!



‹‹ድልም ብዙ ምክር ባለበት ዘንድ ነው›› /ምሳ. 24፡6/፤ ‹‹እርስ በርሳችን እንመካከር›› /ዕብ. 10፡25/!

                              ሐሙስ ታህሳስ 7 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

         ፈተና የምንኖርበት የአሁኑ ዓለም አንደኛው መልክ ነው፡፡ የኖረ ይቸገራል፤ የሚራመድን እንቅፋት ይመታዋል፡፡ መኖር ባይኖር መቸገር ከወዴት አለ? መንቀሳቀስስ ባይኖር እንቅፋት ከወዴት አለ? በዓለም ሳለን መከራ እንዳለብን ይህ አስቀድሞ የተባለ አይደለምን? (ዮሐ. 16፡33)፡፡ ተወዳጆች ሆይ፤ ችግርን ብርቱ ዓይን ሲመለከተውና ደካማ ሲያየው የተለያየ ነው፤ ፈተና በሚያስተውል ሰው ጆሮና በማያስተውል ዘንድ ሲሰማ ሁለቱም ጋር አንድ አይደለም፡፡

       ለችግሮች ጊዜያዊ መፍትሔ ስለ መፈለግ ከምትደክሙ ራሳችሁን በጥንካሬ መገንባት ላይ ጊዜ ውሰዱ፡፡ ፈተና በማንኛውም ጊዜ ሊመጣ ይችላል፡፡ ዳሩ ግን ዛሬ ያልተሠራ ማንነታችሁን በቅጽበት አልያም ውስን በሆነ ጊዜ ውስጥ አትገነቡትም፤ ሁኔታዎችን ለመቀየር ከመድከም ራስን መቀየር ላይ ትኩረት ማድረግ ይበልጣል፡፡ በዚህም ችግር የማይጠጋው ሰው ሳይሆን ችግርን በትክክለኛው መንገድ የሚፈታ ሰው ትሆናላችሁ፡፡  

መልእክት ኀበ ፊልሞና፡፡(1)


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


ሐሙስ ታህሳስ 7 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

(መልእክት ወደ ፊልሞና)

‹‹እምጳውሎስ ሙቁሐ ለኢየሱስ ክርስቶስ፡ (ኤፌ. 31)››!

          የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለመንፈሳዊ ሕይወት ትክክለኛ እድገት መሰረታዊ ነገር ነው፡፡ በስብከትና በንባብ የምናዘወትረውን የእግዚአብሔር ቃል በጥናት መልክ ለመረዳት መሞከር፤ ጊዜ መድቦ መመርመር ከክፍሉ የበለጠ እንድንጠቀም ይረዳናል፡፡ በክርስትና ኑሮአችን ቋሚ የሆነ፤ አማራጭ የማናስቀምጥበት ‹‹ቃሉን የማጥናት ጊዜ›› ቢኖረን እራሳችንን፤ እንዲሁም በዙሪያችን ያሉትን እንጠቅማለን፡፡

         ተወዳጆች ሆይ፤ ያለ እግዚአብሔር ቃል በማንሻገረው የአሁኑ ዓለም ቋሚ ውጊያ እንዲሁም  በዲያብሎስ ሽንገላ መካከል እንደምንመላለስ ላስታውሳችሁ እወዳለሁ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ . . . የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ፤ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው›› /ኤፌ. 6፡17/ ይለናል፡፡ በሚታየው ዓለም የማይታየውን መንፈሳዊ ውጊያ በመንፈስ ሰይፍ ካልሆነ በቀር ድል ልናገኝ አንችልም፡፡

Monday, November 30, 2015

እድል ፈንታችን



ሰኞ ሕዳር 20 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት
ከወንድም እሸቱ

      ጥያቄ፡ - ‹‹ለብዙ  ጊዜ ነገሮች  ላይ እድለኛ  እንደሆንኩ ይሠማኝ ነበረ አሁን ነገሮች በተቃራኒዉ ሆኑብኝ ቀላል ሙከራየ ሁሉ ይከሽፋሉ ምን ይሻለኛል››፡፡

        ወንድም እሸቱ በሙሉ ፈቃደኝነት ችግርህን በጋራ መፍትሔ እንድንፈልግበት ልታካፍለን ስለወደድክ አስቀድሜ ላመሰግንህ እወዳለሁ፡፡ በማስከተል ችግርን በፍጹም ግልጽነት መናገር መቻል የመፍትሔው ትልቅ አካል እንደሆነ እያስታወስኩህ፤ መፍትሔ ልናገኝባቸው እንችላለን ወደምላቸው አሳቦች ከመሄዴ አስቀድሞ ጥቂት ጥያቄዎችን ልጠይቅህ (ለእሸቱ)፡፡

Wednesday, November 25, 2015

የኔታ፡ ኢየሱስ



    እሮብ ህዳር 15 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

ሀ ሁ አቡጊዳ ፊደልን ሊቆጥሩ
ከምምሩ የኔታ ፊት ተኮለኮሉ፤
ትንሽ ምላሶች ይንጫጫሉ
ከወረኛ ዓለም እንዲቀላቀሉ፤
እኒያኛው የሥጋ የኔታ
ዘርግተው የፊደል ገበታ፤
ሲያሻቸው ሲተኙ ሲያንቀላፉ
ሲሻቸው ሕጻናት ሲያስለፈልፉ፤
 ብላቴኖቹ ፊደል ቆጥረው ሲጨርሱ
የምምሩም እግሮች አብረው ተነሡ፤
. . . ሌላኛው የኔታ የጠልጣላ ነፍሴ
ቢያሳስባቸው መዳን መቀደሴ፤
የተግባር ትምህርት ሲጀምሩ
እጆቻቸው በምስማር ተቸነከሩ፡፡

                                       /ከቤተ ፍቅር ቤተሰብ የተላከ/
                      ‹‹ . . . ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ፤›› /ቆላ. 4፡3/!

Friday, November 20, 2015

ድልና ምክር (1)

                                                                      

‹‹ድልም ብዙ ምክር ባለበት ዘንድ ነው›› /ምሳ. 24፡6/፤ ‹‹እርስ በርሳችን እንመካከል›› /ዕብ. 10፡25/!
                            
   አርብ ህዳር 10 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

         ምክክር ወደ መፍትሔ የሚያደርስ የጋራ ችግር ፈቺ ሂደት ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳችን በጽድቅ ላለው ምክር እንደሚጠቅም ተጽፎአል (2 ጢሞ. 3፡16-17)፡፡ በክርስትናው መሰረት ላይ ሆኖ በእለት ከእለት ችግሮቻችን ላይ በጋራ ዝርዝር መፍትሔዎችን ማስቀመጥ፤ መመካከር፤ መጠያየቅ፤ መረዳዳት በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡ ተወዳጆች ሆይ፤ የመፍትሔ ሰዎች መሆን ይብዛላችሁ! 

·        በረከቶቻችሁን ቁጠሩ፡ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ስትሆኑ በኑሮአችሁ ያገኛችኋቸውን በጎ ነገሮች መመልከትን አትዘንጉ፡፡ የፈተና አንዱ መልክ ያላችሁን ሳይሆን የሌላችሁን እንድታስቡ መፈተኑ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች በዚህ መንገድ ይቸገራሉ፡፡ እግዚአብሔር ያደረገላችሁ ይታያችሁ፡፡ በትንሹ እየተቸገራችሁያላችሁት እንኳ በመኖራችሁ እንደሆነ ይታወሳችሁ፡፡ የመኖርን ሌላኛውን ገጽታ መመልከት የምንችለው በሕይወት ስላለን ነው፡፡

Wednesday, November 18, 2015

የፍቅር ዘመቻዎች


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

                                     እሮብ ህዳር 8 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

1. ሁሉንም ሰው አክብር - ክርስቶስ በሁሉም ሰው ውስጥ ይኖራል፡፡ የሌሎች ሰዎችን ስሜት አክብር - እነርሱ የአንተ ወንድሞችና እኅቶች ናቸውና፡፡

2. ስለ እያንዳንዱ ጥሩ አስብ - በማንም ላይ መጥፎ ነገርን አታስብ፡፡ በመጥፎ ሁኔታዎች ውስጥ እንኳን ቢሆን ጥሩ ነገሮችን ለማግኘት ሞክር፡፡

3. ሁልጊዜም ስለ ሌሎች ጥሩ ተናገር - በማንም ላይ ዘለፋን አታድርግ፡፡ በንግግር ካልተገለፀ ቃል የሚመነጨውን ማንኛቸውም ጉዳት አርም፡፡ በሰዎች መካከል ውዝግብና አታካራ እንዲፈጠር ምክንያት አትሁን፡፡

Monday, November 16, 2015

የሕይወት አቅርቦት

(ካለፈው የቀጠለ)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


                                              ሰኞ ህዳር 6 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

       ስለ ሕይወት ስናስብ መለኮታዊነት እና ዘላለማዊነት የብቻው የሆነውን እግዚአብሔርን ልብ እንላለን፡፡ ሕይወት እግዚአብሔር ብቻና ከእርሱ ብቻ ነው፡፡ ሰዎች ስለ እግዚአብሔር የገባቸውን፤ በተረዱት መጠን ቢናገሩ እርሱ እግዚአብሔር ግን ከዚህ ያነሰ አይደለም፡፡ እግዚአብሔርን ልዩ የሚያደርገው ነገር ራሱ እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ሕይወት አስገኝ የለበትም፡፡ ስለ እርሱ ሕልውና ስናወራ እርሱ ራሱ ብቻ መሰረትና ፍጻሜ ነው፡፡

       ዘላለማዊነት ከእግዚአብሔር አንጻር የነገሮች ረጅም ጊዜ መቆየት አይደለም፡፡ መለኮታዊነትም በበላይነት እያስተዳደሩ መዝለቅ አይደለም፡፡ እርሱ ብቻ ዳርቻ በሌለው፤ ስፍራም በማይወሰንለት ልዩነት ከ እና እስከ መቼም ሕያው ሆኖ ይኖራል፡፡ ‹‹ፊተኛ እና ኋለኛው›› (ኢሳ. 44፡6) የእርሱ በቂ ማብራሪያ አይደለም፡፡

       ይህ ከእውቀት ከፍለን እንድናውቅ የተገለጠልን እውነት ነው (1 ቆሮ. 13፡9)፡፡ ይህ አርነት እንድንወጣ በቂ ቢሆንም የምናጣጥመው መንፈሳዊ ነጻነት የመጨረሻ ማብራሪያ ግን አይደለም፡፡ ራሱን እግዚአብሔርን ለምንወርስ (ሮሜ 8፡16) ለእኛ ከመታወቅ የሚያልፍ ነገር ከእርሱ እንደተደረገልን ማመን የሐሴታችን ጥግ ነው፡፡ ገና ከዚህ ሕይወት ጋር ለማይቆጠር ጊዜ፤ በማይወሰን ስፍራ እንኖራለን፡፡ እግዚአብሔር ብቻ ያልተፈጠረ ሕይወት ነው!

       ቅዱሱ መጽሐፍ ሕይወት መገኛዋ ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር እንደሆነ ያስረዳናል፤ ‹‹በአደባባይዋም መካከል ከእግዚአብሔርና ከበጉ ዙፋን የሚወጣውን እንደ ብርሌ የሚያንጸባርቀውን የሕይወትን ውኃ ወንዝ አሳየኝ።›› (ራእ. 22፡1)፡፡ የእግዚአብሔር ሕይወት ራሱ እግዚአብሔር ነው፤ የእኛም ሕይወት እርሱ ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር ነው፡፡ ብቻውን ጸንቶ የሚኖር ሕይወት፤ ባህርዩ ሊቀየር የማይችል ሕይወት እግዚአብሔር አምላካችንና አባታችን ነው፡፡

       ተወዳጆች ሆይ፤ የእግዚአብሔር ሕይወት ለሞት የሚገዛ ሕይወት አይደለም፡፡ ከሕልውና በቀር መጥፋት አያብራራውም፡፡ ሽንፈት ድካም፤ መለወጥ መናወጥ አይገልጸውም፡፡ ይህ ሕይወት ከራሱ ከእግዚአብሔር ካልሆነ በቀር መልአክ ቢሆን አይሰጠንም፡፡ የሥጋ ለባሽ የጥረቱ ውጤት ሊሆንም አይችልም፡፡ በምንኖርበት ዓለም እንኳ ሕይወት ከእግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡

Monday, November 9, 2015

የሕይወት አቅርቦት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


ጥቅምት 29 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት
 /ፊል. 2፡14-15/

         በምጣኔ ሀብት ባለ ሙያዎች ዘንድ የፍላጎትና የአቅርቦት መጣጣም ጉዳይ የሁል ጊዜ ርዕስ ነው፡፡ የሰዎች ፍላጎት ሰፊ በሆነበት ሁኔታ ለዚያ አሳማኝ መሻት በቂ የሆነ ምላሽ መስጠት የሚጠበቅ እንደ መሆኑ የምድር መንግሥታት ለዜጎቻቸው ይሠራሉ፡፡ እግዚአብሔር የሰማያትና የምድር ገዥ ነው፡፡ የሁሉ ዓይን ተስፋ የሚያደርገው እርሱ (መዝ. 144፡15) በተለየ ሁኔታ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ልጁ ለሆኑት (ዮሐ. 1፡12) በሚያስፈልጋቸው ነገር ሁሉ ያስባል፤ ያደርጋልም (ፊል. 4፡19)፡፡

         የእግዚአብሔርን የዘላለም አሳብና የልብ ምክር በመስማትና በማስተዋል፤ ደግሞም በመታዘዝ ወደ እምነት የመጡትን (ሮሜ 10፡17) በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ የሚሰየምበት (ኤፌ. 3፡14) እግዚአብሔር እንደ አባት ይመግባል፤ ይንከባከባል፤ ያሳድጋል (1 ቆሮ. 3፡6)፡፡ እርሱ ጌታ ሕይወትን የሚሰጥ ብቻ ሳይሆን የሚያበዛም ነው (ዮሐ. 10፡10)፡፡ የዘላለምን ሕይወት ከእግዚአብሔር ጸጋ በክርስቶስ ኢየሱስ ያገኙ ሁሉ (ሮሜ 6፡23) ለዚህ ሕይወት አስፈላጊ የሆነውን ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት በመቅረብ ያገኛሉ (ዕብ. 4፡16)፡፡     

        ተወዳጆች ሆይ፤ እግዚአብሔር ሰውን ከመፍጠሩ አስቀድሞ ለሚፈጥረው ሰው አስፈላጊው የሆኑትን ነገሮች ሁሉ እንዳዘጋጀ (ዘፍ. 1)፤ በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት መሆናችንን (2 ቆሮ. 5፡17) ተከትሎ ያለን ኑሮም እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ማድረግ ነው (ኤፌ. 2፡10)፡፡ እግዚአብሔር ታላቅና ድንቅ አምላክ ነው (መዝ. 85፡10)፡፡ የእርሱ እጅ ሥራ የሆነው ሰው ለቀጣዩ አሁን የሚያቅድ፤ ያውም ይድረስ አይድረስ በማያውቀው ጊዜ ላይ አስቀድሞ የሚዘጋጅ ሆኖ ሳለ እጅግ ኃያል የሆነው እግዚአብሔር እርሱ እንዴታ?

Friday, October 2, 2015

‹‹የመጽናናት ሁሉ አምላክ››


      (2 ቆሮ. 1፡3)
 
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አርብ መስከረም 21 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

          በቅዱሱ መጽሐፋችን ‹‹አጽናኑ፤ ሕዝቤን አጽናኑ፡ ይላል አምላካችሁ፡፡›› /ኢሳ. ፡1/ ተብሎ እንደተጻፈ፤ ክርስቲያኖች በፈተናና በመከራቸው እርስ በእርስ የሚጽናኑበት ‹‹የርኅራኄ አባትና የመጽናናት ሁሉ አምላክ›› እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ 
          እርሱ አምላካችን የዘላለም አምላክ፤ የምድር ዳርቻ ፈጣሪ፤ የማይደክም የማይታክት፤ ማስተዋሉም የማይመረመር፤ ሰማያትን የፈጠረ የዘረጋቸው፤ ምድርንና በውስጥዋ ያለውን ያጸና፤ በእርስዋ ላይ ለሚኖሩ ሕዝብ እስትንፋስን፣ ለሚሄዱባትም መንፈስን የሚሰጥ ነው፡፡   

Saturday, September 19, 2015

ከማያምንም የከፋ፡

                 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ቅዳሜ መስከረም 8 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት 

         ‹‹ነገር ግን ለእርሱ ስለ ሆኑት ይልቁንም ስለ ቤተ ሰዎቹ የማያስብ ማንም ቢሆን፥ ሃይማኖትን የካደ ከማያምንም ሰው ይልቅ የሚከፋ ነው።›› /1 ጢሞ. 5፡8/፡፡

        ቤተ፡ ሰብ፤ የብዙ ነገሮች መሠረት እንደ ሆነ በብዙዎች ዘንድ ይነገራል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም እንዲሁ ለቤተ፡ ሰዎች ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል፡፡ በብሉይ ኪዳን ቤተ፡ ሰብ የሚለው፤ በአዲስ ኪዳን ቤተ ሰዎች በማለት ተጽፎ እናነባለን፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ትኩረት ከሰጣቸው ነገሮች አንዱ በቤተ፡ ሰዎች መካከል ያለው ግንኙነት ተጠቃሽ ነው፡፡

        የመጽሐፍ ቅዱሳችን የመጀመሪያ ክፍል የዘፍጥረት መጽሐፍ ስለ ስድስት ቤተ፡ ሰዎች ማለትም አዳም፤ ኖኅ፤ አብርሃም፤ ይስሐቅ፤ ያዕቆብና ዮሴፍን ቤተሰባዊ ኑሮ የሚተርክና ለኪዳኑ ታማኝ የሆነውን እግዚአብሔር የሚያሳየን ድንቅ መጽሐፍ ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ እንደ አቤል ያለውን የእምነት ሰው፤ ደግሞም እንደ ቃየል ያለውን የሞት ልጅ የምናገኝበት ብዙ ትኩረትና ማስተዋላችንን የሚጠይቅም ክፍልም እንደሆነ ልብ እንላለን፡፡

Sunday, September 13, 2015

ዘመን እንደ ዮሐንስ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ቅዳሜ መስከረም 1 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት  

           በቤተ፡ ክርስቲያን 2008 የምሕረት ዓመት ‹‹ዘመነ ዮሐንስ›› ይባላል፡፡ በአዲስ ኪዳን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ወንጌላቱ በተቀመጡበት ቅደም ተከተል በአራት ዓመት አንድ ጊዜ አንዱ ወንጌላዊ ዘመኑ ይሰየምበታል፡፡ ብዙ ሰዎች ልብ ባይሉትም ዘመን በተፈራረቀ ቁጥር አንዱ ወንጌላዊ ለሌላው እየተቀባበለ ዓመቱ በወንጌል ጸሐፊዎቹ ስም ይጠራል፡፡

Friday, August 21, 2015

ፍቅር እና ጀበና


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አርብ ነሐሴ 15 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

እዚያ . . . ቡና ጠጡ፤
አሉባልታ አድምጡ።
ብዬ ከወዳጆቼ ተሰባስቤ፤
ለወሬ ተሰናድቶ ቀልቤ።
የሰው ሥጋ ስንቋደስ፤
ስንቀቅል ስንጠብስ።
ከፍም የተገናኘው ሸክላ፤
በእሳቱ ነበልባል ሲበላ።
ድንገት . . . እፍ . . . እፍ . . . ኧረ ገነፈለ፤
ቡናው ከጀበናው ዘለለ።
እኛ ስናወራ እሳቱ አይሎ፤
ጀበናው የውስጡን አወጣ አግተልትሎ፡፡
እዚህ . . . ቡና ጠጡ፤
ቃሉን አድምጡ። 
ብዬ ወዳጆቼን ሰብስቤ፤
ለቃሉ ተሰናድቶ ቀልቤ።
የሰው ነፍስ ስንናጠቅ፤
ከክፉ ሥራ ስናላቅቅ።
ከፍም የተገናኘው ሸክላ፤
በሳቱ ነብልባል ሲበላ።
ድንገት . . . እሰይ . . . እሰይ . . . ገነፈለ፤
ፍቅር ከጀበናው ዘለለ።
ከተሰባሪው ገል ገላ፤
ከእኔነቴ ሸክላ።
የመለኮት እሳት በዝቶ፤
ውስጤን አግሎ አፍልቶ።
እንደ ፈሳሽ ምንጭ፤
ከሰዎች ሲሰራጭ።
የሕይወት ቡና ቢያጠጣ፤
ከሸክላነታቸው ሸክላ ወጣ።
እናንተም የፍቅሩ ቁራሾች፤
የመለኮት እሳት ተካፋዮች።
ከፍቅር ጀበና ገንፍሉ፤
ከሸክላነታችሁ ውጡና ዝለሉ።

                                 ‹‹ . . . ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ፤›› /ቆላ. 4፡3/!
                  

Friday, August 14, 2015

ስፍራችሁን ያዙ

(ካለፈው የቀጠለ)
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አርብ ነሐሴ 8 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

      ‹‹ነጽር ኀበ አይ መካን አዕረጋ ለቤተ ክርስቲያን ዘከመ ይእቲ ኩለን ሰሐባ በጥበብ እምሉዓሌ፡፡ ወክመዝ አዕረጋ ኀበ ልዕልና ዐቢይ÷ ወለዝንቱ ዘውእቱ እምኔነ አንበሮ ዲበ ዝንቱ መንበር÷ ወለነሂ ዓዲ ለቤተ ክርስቲያን ስሐበነ እግዚአብሔር ኀቤሁ በከዊኖቱ ርእሰ ዚአነ እስመ ውስተ መካን ኀበ ሀሎ ርእሰ ህየ ይሄሉ ሥጋ ቤተ ክርስቲያን አካሉ እንደ መሆንዋ መጠን ወዴት ከፍ ከፍ እንዳደረጋት አስተውል፡፡ ከላይ ሆኖ በጥበብ ወደ እርሱ አቀረባት እንደዚህ ወዳለ ክብርም አወጣት ከእኛ ወገን የሆነውን /ከመለኮት ጋር የተወሐደውን/ ትስብእትንም በዚያ ዙፋን በቀኙ አስቀመጠው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሆንነውን እኛንምርስቶስ ራሳችን በመሆኑ እግዚአብሔር ወደ እርሱ ሳበን÷ ራስ ካለበት ሕዋሳት ይኖራሉና››      

/ሃይማኖተ አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ፤ 67÷39/