Tuesday, December 30, 2014

ዕድሜህ ስንት ነው?

              በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ማክሰኞ ታህሳስ 21 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

     የሰው የተሰፈረ ዕድሜ የዘላለም እግዚአብሔር ስጦታ ነው፡፡ ሰው ስለተዋደደ የማይጨምረውና የማያዝበት ልዩ በረከት ልንኖርበት የተሰጠን ዘመናችን ነው፡፡ የሥጋ አባታችን አልያም እናታችን የቱንም ያህል ቢወዱን ከዕድሜያቸው ቀንሰው በእኛ ላይ አይጨምሩልንም፡፡ እየኖርን እንደሆነ በተሰማን ጊዜ ሁሉ እያኖረን ያለውን አምላክ ቸል ማለት በደል ነው፡፡ በዚህ መንገድ ለተባረክንበት መባረክ የመጀመሪያው ምላሽ ይህንን እውቅና መስጠት ነውና፡፡ ስለ ስጦታው በቂ ማስተዋል በውስጣችን ከሌለ፤ ለሰጪውም ሆነ ለስጦታው ክብር አይኖረንም፡፡ ተቀብለን ሰጪውን ልብ አለማለት መንፈሳዊ ድንዛዜ ነው!

      ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ዕድሜ ሰዎች ‹‹ስንት ነው?›› ጥያቄ ሲያስጨንቃቸው፤ አሳንሰው ሲናገሩ አልያም ባልሰማ ሲያልፉ ብዙ ጊዜ መመልከት የተለመደ ነው፡፡ እንዲህ ያሉ ሰዎች ልኩን ለመናገር የሚቸገሩበትን የስነ ልቦና ትንታኔ ለጊዜው እንተወውና፤ በጀመርንበት መንፈሳዊ ቅኝት ወደ ፊት ለማየት እንሞክር፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ረጅም ዕድሜ የኖሩ፤ እንዲሁም አጭር ዘመን ኖረው ያለፉ ሰዎችን እናገኛለን፡፡ ለዚህ አሳብ በዘፍጥረት ምዕራፍ አምስት ላይ የምናገኛቸውን አባትና ልጅ እንይ፡፡

Tuesday, November 18, 2014

የጸናውን ማሰብ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
                        
ኅዳር 8 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

       በአንድ ሰው ውስጥ ያለው ትልቁ ኃይል ‹‹አሳብ›› እንደ ሆነ ብዙዎች ይስማማሉ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ በብርቱ የምናስበውን ያንን የመሆን ዕድላችን ሰፊ ስለሆነ፤ ሰው አስተሳሰቡ መጠበቅ እንዳለበት ይመከራል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል የእውነተኛ አሳብ እውነተኛ ምንጭ ነው፡፡ እምነት ከመስማት ከሆነ የምንሰማውና የምንስማማው እውነተኛ አሳብ አለ ማለት ነው (ሮሜ. 10÷17)፡፡ ያም አሳብ ከዘላለም የሆነው የእግዚአብሔር አሳብ ነው (ኤፌ. 3÷11)፡፡
      
       ቃሉ ‹‹በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ›› (መክ. 12÷1) እንደሚል፤ የጽናት ደጀኑ እግዚአብሔርን ማሰብ ነው፡፡ በጉብዝናችሁ ዘመን የቆማችሁለት አሳብ ከሌለ ማንኛውም አሳብ ይጥላችኋል፡፡ የተሰበሰባችሁበት ዘላለማዊ ጥላ ከሌለም፤ የጊዜው ያባዝናችኋል፡፡ በወጣትነታችሁ የያዛችሁት እውነት ከሌለ ሐሰት ይገዛችኋል፡፡ በምቾቶቻችሁ ውስጥ ያጌጣችሁበት ጽድቅ ከሌለ ርኩሱ ይሸፍናችኋል፡፡ በጤና ጉብዝና፤ በእውቀት ጉብዝና፤ በሀብት ጉብዝና፤ በወዳጅ ጉብዝና እግዚአብሔርን ካልመረጣችሁ፤ ለእግዚአብሔር ካልቆረጣችሁ ዓለም ያሰላቻችኋል፡፡

       አሳብ ከየትኛውም ልማድ በላይ ነው፡፡ አሳባችን በልማዶቻችን ላይ የበላይ ካልሆነ፤ ለልማድ ባሪያ መሆናችን የተገለጠ ነው፡፡ በሕይወታችሁ ውስጥ ስታስቧቸው ደስታን የሚፈጥሩላችሁና ብርታት የሚሆኗችሁን ሰዎች ወይም ሁኔታዎች እስቲ ወደ አእምሮአችሁ አምጡና በወረቀት ላይ አስፍሯቸው፡፡ በመቀጠልም በተቻለ መጠን  ምክንያታችሁን አንድ በአንድ ለመጥቀስ ሞክሩ፡፡ 

Sunday, October 26, 2014

ከከፋን የከፋ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ጥቅምት 16 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

         ወንጌል ያስተማርኳትን አንዲት ሴት በቢሮዬ መንገድ ላይ አግኝቻት፤ በፀጉሯ መንጣት፤ በሰውነቷ መግዘፍ፤ በፊቷ መሸብሸብ ስገረም፤ ‹‹የነገርከኝ ቃል ግን አላረጀም›› አለችኝ፡፡ ታዲያ ስለ ባለቤቷና ልጆቿ እየጠየኳት፤ በመሐል ‹‹ምን ሆነህ ነው? ፊትህ ደህና አይደለም›› እያለች ምራቋን እጇ ላይ እንትፍ ብላ ለእኔ የማይታየኝን እሷ የምታየውን ከፊቴ ላይ ታብሳለች፡፡ በእርግጥ በጊዜው ያዘንኩበት ነገር ቢኖርም፤ ያ ከአሳቤ በስተ ውስጥ የነበረ ነው፡፡ ሴቲቱ ፊቴ ላይ ምን ታይቷት እየደጋገመች ምራቅ እንዳጠገበችው ባላውቅም፤ በጊዜው ግን ቅንነቷን እንዳደነቅሁ አስታውሳለሁ፡፡ ምንም እንኳን ለጭርት ወጪ ብታስወጣኝም ማለት ነው፡፡

           ሴቲቱ እንደ ከፋኝ እያወራች በምራቅ ጉንጬን አራሰችው፡፡ በጊዜው እኔ ያዘንኩበት ነገር እድሜው አጭር፤ ክብደቱ ቀሊል፤ መፍትሔው ግልጽ ነበር፡፡ ደግሞ ‹‹እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን።›› የሚለው የታመነ ቃል ልቤን ሞልቶት ነበር፡፡ የከፋኝን ለማስወገድ /በእርሷ ግንዛቤ/ ከከፋኝ የከፋ ነገር አደረገች፡፡ እንግዲህ ይህ ከሁለት አመታት በፊት የሆነ አጋጣሚ፤ በዚህ ርዕስ ዙሪያ ልጽፍ ሳስብ ትዝ አለኝ፡፡ ለመነሻም እንዲሆን አሰብኩ፡፡

Friday, October 17, 2014

አብርሃም እንዲህ አላደረገም


ጥቅምት 7 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

‹‹አብርሃም እንዲህ አላደረገም›› /ዮሐ 8÷40/!

       የተሻለ ሰምቶ የተሻለ መናገር፤ የበለጠ አይቶ የበለጠ መሥራት በሰው ልጆች ሕይወት ውስጥ የማይቋረጥ ቅብብሎሽ ነው፡፡ ይህንንም አበው ‹‹ትውፊት›› ወይም ጤናማ መወራረስ ይሉታል፡፡ ያለንን መቀባበል መልካም ነው፡፡ የምንቀበለው ሁሉ ግን መልካም ሊሆን አይችልም፡፡ ከእግዚአብሔር የተቀበልነውን ሕሊና ሥራ ላይ ከምናውልበት መንገድ አንዱ መምረጥ ስለሆነ፤ እንደ ባለ አእምሮ አስተውለን ልንመርጥ  ያስፈልገናል፡፡ የሚረባንን ከማይረባን መለየት የምንችልበት መንሽ ደግሞ ቅዱስ ቃሉ ነው፡፡

       መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹አባትህን ጠይቅ ይነግርህማል›› /ዘዳ 32÷7/ የሚል መጽሐፍ ብቻ አይደለም፡፡ ለአንዳንድ ልብ የመጽሐፉ ሙሉ ጭብጥ ከዚህ አይዘልም፡፡ ነገር ግን ‹‹ማስተዋል ይጋርድሃል›› /ምሳ 2÷11/ ተብሎ እንደ ተፃፈ፤ የቃሉን ሙሉ ገጽታ መመልከት ያስፈልጋል፡፡ በኑሮአችንም እንዲሁ ነው፡፡ ማስተዋል ከከንቱ ኑሮ፤ ውልና ማለቂያ ከሌለው ጥረት፤ ከስህተት ጎዳና ይጠብቃል፡፡ ምድሪቱ ላይ እኛን አድራሻ አድርጎ ከሚመጣ ከየትኛውም ክፉ ትግል፤ ከቅርብም ከሩቅም ባላንጣ መጋረድ በቃሉ ነው፡፡ ጌታ በሊቀ ካህናትነት ጸሎቱ ‹‹በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው።›› /ዮሐ 17÷17/ እንዳለ፤ ከየትኛውም ጠላትነት የምንጠበቅበት አጥር ቅዱስ ቃሉ ነው፡፡ በዚህም ውስጥ የምናስተውለው ትልቁ ነገር ቅዱሱን እግዚአብሔር ነው፡፡

       ካለፉት በሕይወት ኖሮ መማር እጅግ ጤናማ ነው፡፡ ሌሎች ቀድመውን ካዩት መማር እየቻልን ‹‹እስክናይ›› ብለን ግትር አንሆንም፡፡ ነገር ግን የቀደሙን ያዩት ሁሉ ልክ፤ የሠሩት ሁሉ እጅግ በጣም ጥሩ እንደ ሆነ ማሰብ ደግሞ ጤናማ አይደለም፡፡ ኑሮአችን ከዘላለም እስከ ዘላለም ያው /መዝ 89÷2/ በሆነው እግዚአብሔር ይመዘናል፡፡ በተሰጠን የእውነት ቃል /ኤፌ 1÷13/ ሁሉም ይፈተሻል፡፡ ሐዋርያው ጴጥሮስ ‹‹ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር›› /1 ጴጥ 1÷19/ ሲል፤ ውርስ ሁሉ ጤናማ አለመሆኑን ያስገነዝበናል፡፡ ከሙግቶቻችን አልፈን ማየት ካልቻልን ለእኛ መዳን እንዴት ጭንቅ ነው?

Tuesday, October 14, 2014

ቱንቢ (plumbline)



ጥቅምት 4 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

‹‹እንዲህም አሳየኝ እነሆም፥ ጌታ ቱንቢውን ይዞ በቱንቢ በተሠራ ቅጥር ላይ ቆሞ ነበር››
/አሞ 7÷7/

        በአዲስ ኪዳን መጻሕፍት የታሪክ ክፍል በሆነው የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ከምንማራቸው መንፈሳዊ ትምህርቶች መካከል ትጋት አንዱ ነው፡፡ ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር ፊት የሚተጉበትን ነገር መመርመርና መመዘን አለባቸው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ስለሆነ አይመረመርም፡፡ የሰው ፍለጋና ጥረትም አያገኘውም፡፡ ዳሩ ግን ሥጋ ለባሽ ሁሉ ሕያውና ጻድቅ በሆነው በእርሱ በእግዚአብሔር ፊት ቃልና ኑሮው ይመዘናል፡፡ በእውነት ላይ የተመሰረተው ‹‹ይበል›› ተብሎ ይሁንታን ሲያገኝ፤ እንደ ዘላለም ምክሩና እንደ ጌታ ልብ ያልሆነው ሁሉ ግን ሁሉን እንደ ፈቃዱ በሚያደርግ ሉዓላዊ አምላክ ዙፋን ፊት በጽድቅ ይዳኛል፡፡

        እግዚአብሔር እውነቱን የሚለካ ሌላ እውነት የሌለ እውነተኛ፤ ጽድቁን የሚመዝን ሌላ ሚዛን የሌለ ጻድቅ፤ ቅድስናውን የሚተያይ ሌላ ቅድስና የሌለ ቅዱስ አምላክ ነው፡፡ ሁሉ በእርሱ ተፈጥሮአልና፤ ከሆነውም ሁሉ ያለ እርሱ የሆነ አንድ ስንኳ የለምና ሁሉን የሚመዝን እርሱ ነው፡፡ እውነተኛ አምላክ የሆነ እርሱ ብቻ /ዮሐ 17፣3/ የቃልና የኑሮአችን ቱንቢ በእጁ አለ፡፡ እርሱ እውነተኛ አምላክ ነው፡፡ ሁሉ በእርሱ ይመዘናል፡፡ ‹‹እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል? የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው፥ የሚኰንንስ ማን ነው?›› /ሮሜ 8፥33/ ተብሎ እንደ ተፃፈ፤ እግዚአብሔር ነገሮቻችንን ሊመዝን፤ ሊያጸድቅና ሊኮንን እውነተኛ ዳኛ ነው /መዝ 7÷11/፡፡

Saturday, October 4, 2014

ብዙ ኃይል


                            መስከረም 24 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

‹‹በጻድቅ ሰው ቤት ብዙ ኃይል አለ፤ የኃጥእ ሰው መዝገብ ግን ሁከት ነው።›› 
(ምሳ. 15÷6)፡፡

         በሰው ልጆች አኗኗር ውስጥ ኃይል እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ በኃይል እጦትና እጥረት ሰዎች ያለ መብራት በጨለማ ይሄዳሉ፤ ያልበሰለ በጥሬው ይበላሉ፡፡ ሰዎች በአቅም ማነስ ምክንያት ለተግባር ብዙ ይቸገራሉ፡፡ ኃይል የማይገባበት የኑሮ ክፍል የለም፡፡ ብዙ ነገሮች በብዙ ኃይል ጭምር የሚተገበሩ ናቸው፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ በመንፈሳዊው ዓለም ስላለው ከፍተኛ ኃይል ይነግረናል፡፡ ጠቢቡ በዘመኑ ያስተዋለውን ባካፈለበት በዚህ ክፍል ላይ ጻድቅ ቤት ውስጥ ብዙ ኃይል እንዳለ ሲነግረን፤ በኃጢአተኛ መዝገብ ውስጥ ግን ሁከት አለ ይለናል፡፡

        ጠቢቡ ጻድቅና ኃጥእን፤ ቤትና መዝገብን፤ ኃይልና ሁከትን እነዚህን ሁለት ነገሮች ከሰው አንፃር በንጽጽር አቅርቦልናል፡፡ ጽድቅ የሚለው አገላለጽ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነትን ያገኘ እውነተኛ ማንነትን ሲያሳይ፤ ኃጥእ የሚለው አገላለጽ ደግሞ ከእግዚአብሔር ጋር ጸብ ውስጥ ያለና መንገድ የሳተ  ማንነትን ያመላክተናል፡፡ ቤት ልንኖርበትና ልንጠለልበት ያለንበትን ክልል ሲያሳይ፤ መዝገብ አንድ ሰው የሚሰበስበውን የሚያኖርበትን ስፍራ ያመለክተናል፡፡ ብዙ ኃይል የሚለው አገላለጽ ጽድቅ የሚለውን አዎንታዊ ቃል ተከትሎ የመጣ እንደ መሆኑ በዚያው መንገድ የምንመለከተው ብርቱ ነገር ሲሆን፤ ሁከት ደግሞ የደፈረሰ ያልጠራ፤ ሰላም የሌለበትን ነገር ያስረዳናል፡፡

Friday, September 26, 2014

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር፡


/ካለፈው የቀጠለ/
                  (መዝ. 123÷1-8)
                          መስከረም 16 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

        ከእናንተ ጋር ያላችሁ ምንድነው? መቼም አንድ ነገር እያለን፤ ነገር ግን እንዳለን ባናውቅ ይህ እጅግ ያሳዝናል፡፡ የፍቅር ሐዋርያው ዮሐንስ ‹‹የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ›› /1 ዮሐ. 5÷13/ ሲል፤ የዘላለም ሕይወትን የተቀበሉ ግን ደግሞ ይህንን የተሰጣቸውን ሕይወት ያላስተዋሉ ክርስቲያኖችን ልብ እንላለን፡፡ ተወዳጆች ሆይ፤ ይህንን አለመረዳት ትርጉሙ ቀላል አይሆንም፡፡ ኪሳራውም እጅግ የከፋ ነው፡፡

       የእግዚአብሔር ሰዎች ያላቸው ትልቁ ‹‹እግዚአብሔር›› ብቻ ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር አለመሆኑ ምን ሊያመጣ እንደሚችል በተረዳው መጠን ይናገራል፡፡ በዚህ መዝሙር ውስጥ ያሉትን አሳቦች በሁለት ከፍለን ልናያቸው እንችላለን፡፡ የመጀመሪያው ካለፈው ነገር ጋር የተያያዘ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ከመጪው ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ባለፈው ጊዜ ካለፈው ኑሮ ጋር የተያያዘውን አሳብ ማየት ጀምረን ነበር፡፡ በዚህም ክፍል አሳቦቹን በዝርዝር እናያለን፡፡

Thursday, September 11, 2014

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር፡

                 (መዝ. 123÷1-8)

                           መስከረም 1 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

     ስላልተሳኩልን ነገሮች ማስታወስ ለሰው እያደር የሚመረቅዝ ቁስል ነው፡፡ ምስጋናችንን ምሬት፤ እልልታችንን ጩኸት፤ ደስታችንን ዕንባ እየቀደመው የምንቸገርበትም ርዕስ ይህ ነው፡፡ ተወዳጆች ሆይ፤ ወደ ኋላ መለስ ብላችሁ ያለፈውን ስታስቡ ለልባችሁ የቀረው ነገር ምንድነው? ያጣችሁት ወይስ ያገኛችሁት? የተደረገላችሁ ወይስ የተወሰደባችሁ? ምሬት ወይስ ሐሴት? የትኛው ሚዛን ይደፋል? ‹‹ዘመን መለወጡ፤ በእድሜ መባረኩ፤ ተጨማሪ ዕድል ማግኘቱ ልባችንን በደስታ ያጠግባልን?›› ብለን እንደ ክርስቲያን ብንጠይቅ ጥያቄያችን ጥያቄን፤ ጥማታችን የበለጠ መጠማትን ያገናኘናል፡፡ ያለ እግዚአብሔር ሕልውና አለመኖር ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር አለመሆናቸውን ሲወቅሱ፤ እግዚአብሔር በዚያም ውስጥ ከእነርሱ ጋር በመሆኑ ግን አይደነቁም፡፡ የተዋችሁት ከያዛችሁ፤ ቸል ያላችሁት ካልረሳችሁ ከዚህ የሚበልጥ ምን የምስጋና ርዕስ አለ?

Wednesday, September 10, 2014

አንተ ግን፡

 ‹‹አንተ ግን፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ የምነግርህን ስማ እንደዚያ እንደ ዓመፀኛው ቤት ዓመፀኛ አትሁን አፍህን ክፈት የምሰጥህንም ብላ።››  /ሕዝ. 28/

Saturday, August 16, 2014

ፍቅርም እንደዚህ ነው!

                       Please Read in PDF: Fikirm Endezih New
                             
                                ነሐሴ 10 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

      ‹‹የሕይወታችን ምስጢር በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተገለጠ መጽሐፍ ከሆነ ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ሆኖታል፡፡ ያለፈው፤ የአሁኑ እና የወደፊቱ ሕይወታችን ሁሉ በእርሱ ተገልጧል፡፡ ያለፈው ሕይወታችን በእርሱ ስቃይና መከራ፤ የአሁኑ በእርሱ ጸጋ እና ምሕረት የተገለጠ ሲሆን፤ የወደፊቱ ደግሞ በዘላለማዊው ሕይወት ይገለጣል›› (ቶማስ አኩይናስ)፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በማመናችን የምናገኘውን ትልቅ ነገር ሲናገር ‹‹ሕይወት›› በማለት ይገልጸዋል፡፡ የፍቅር ሐዋርያው ‹‹የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ›› (1 ዮሐ. 5÷13) ሲል፤ የዘላለም ሕይወት ያላቸው ግን ያንን ያገኙትን የዘላለም ሕይወት የማያውቁትን ሰዎች እያስታወሰ ነው፡፡ እራሳችንን መርዳት በማንችልበት ‹‹ሙታን›› የተሰኘ ኑሮ ውስጥ ስንኖር ሳለ፤ ሕይወት እንዲሆንልን እንዲበዛልንም (ዮሐ. 10÷10) የእግዚአብሔር ልጅ በሥጋ ተገለጠ፡፡

     ተወዳጆች ሆይ፤ የዘላለምን ሕይወት እንዳገኛችሁ፤ ይህም ለእናንተ በክርስቶስ ክርስቲያን በመሆናችሁ እንደ ተሰጠ ታውቃላችሁን? ይህንን አለማወቅ አጉል ነዋሪ ያደርጋል፤ ተስፋ መቁረጥንና ለሞት ባርያ መሆንን ያመጣል፡፡ አዲስ ኪዳንን በደንብ ስናጠና ከምናስተውለው ነገር አንዱ ‹‹እግዚአብሔር ለእኛ የዘላለም ነገር እንዳለው›› ነው፡፡ ከእርሱ ጋር ሊኖረን የሚችለው ግንኙነት ከዚህ ባነሠ ነገር ላይ የተመሠረተ አይደለም፡፡ ሰው ኃጢአትን በማድረጉ፤ ተከትሎ የመጣው ደመወዝ ‹‹የዘላለም ሞት›› ነው (ሮሜ. 6÷23)፡፡ የዘላለም አባት እግዚአብሔር (ሮሜ. 16÷25)፤ የዘላለም ልጁን (ሮሜ. 9÷5)፤ በዘላለም መንፈስ (ዕብ. 9÷14) ለእኛ ምትክ አድርጎ በመስጠቱ የዘላለም ሕይወትን በጸጋ ተቀበልን (ኤፌ. 2÷5)፡፡ ይህም እግዚአብሔር ለእኛ ያለው የዘላለም አሳቡ ነው (ኤፌ. 3÷12)፡፡ እግዚአብሔር ለእኛ የማይቆጠር ነገር ማድረጉ ምንኛ ድንቅ ነው?

Friday, July 18, 2014

ከፍ ብሎ መቀመጥን፤ ዝቅ ብሎ በመቀመጥ ሞክረው!

                             
                   ሐምሌ 11 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

      እውነተኛ ወዳጅ የሚታወቀው፤ የወዳጅነት መፈታተኛ በሆነው በጭንቅና በመከራ ጊዜ ነው፡፡ ቁጣ የአዋቂውን ሰው ዕውቀት ያጠፋል፡፡ ቁጣና ትውኪያ ካሰቡት አያደርስም የሚባለው ስለዚህ ነው፡፡ ራሱን በራሱ የሚያመሰግን ሰው ራሱን ባይታመንና ሰው የማያመሰግነው መሆኑን ስለሚያውቅ ነው፡፡ እንዲሁም እርሱ የሚሠራው ሥራ ሁሉ በሰዎች ዘንድ የማይመሰገን መሆኑን ስለሚያምን ነው፡፡ በተድላ ደስታ መኖር ከተፈለገ ከወንድም ቅናትና ከጠላት ሽንገላ መጠንቀቅ ነው፡፡ ጊዜ ሳለው አለሁልህ ማለትን ለማያውቅ ጊዜ ሲከዳው አለሁልህ የሚለው አይገኝም፡፡ ጠባየ ክፉ ለሆነ ሰው ፍቅር አይስማማውም፡፡ ወዳጁ የሚከብደው ሰው ሸክሙ የቀለለ ነው፡፡

      አንድ ፈላስፋ ከወንድምህና ከወዳጅህ ማናቸውን ትወዳለህ? ቢሉት ወዳጄ ከሆነ ወንድሜ ነው አለ፡፡ ሆኖም ከበጎ ባልንጀራ መልካም ጠባይ ይበልጣል አለ፡፡ ያልያዘውንና የማያገኘውን የሚመኝ ሰው የያዘውንና ያለውን እስከ ማጣት ይደርሳል፡፡ ጥቂት ገንዘብ ከምስጋና ጋር ታላቅ ሃብት ነው፡፡ የማይችለውን እሸከማለሁ የሚል ሰው ለመሸከም የሚችለውንም ያጣል፡፡ በሐሰት ከመናገር በእውነት ድዳ መሆን በዓመፅ በሰበሰቡት ገንዘብ ሃብታም ከመሆን ጽሮ ግሮ ባገኙት ገንዘብ ድኻ መሆን ይሻላል፡፡ ሃብት በማያውቅበት ሰው ዘንድ በሞተ ሰው መቃብር ላይ ምግብን እንደ ማስቀመጥ ያለ ነው፡፡

Sunday, May 25, 2014

ቀላል ነው (ካለፈው የቀጠለ)

                   Please Read in PDF: Kelal new (yeketele)
                        እሁድ ግንቦት 17 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

     ‹‹ታላላቆችም ብላቴኖቻቸውን ወደ ውኃ ሰደዱ፤ ወደ ጕድጓድ መጡ፤ ውኃም አላገኙም፥ ዕቃቸውንም ባዶውን ይዘው ተመለሱ፡፡ አፈሩም ተዋረዱም ራሳቸውንም ተከናነቡ።›› (ኤር. 14÷3)፡፡

        አቤት ምድረ በዳ፤ አቤት ቃጠሎ፤ አቤት የውኃ ጥም፤ አቤት አቅም ማጣት፤ አቤት ሥጋት፤ አቤት መጨካከን፤ አቤት መጣደፍ፤ አቤት መተራመስ፤ አቤት አዙሪት፤ አቤት መዛል፤ አቤት እፍረት፤ አቤት መዋረድ፤ አቤት መደበቅ፤ አቤት አለመፈናፈን፤ አቤት ማለክለክ፤ አቤት የዕንባ ጅረት፤ አቤት የዓይን መጠውለግ፤ አቤት የማይቆጠር በድን፤ አቤት የተማሱ ጉድጓዶች፤ አቤት አፉን የከፈተ መቃብር፤ አቤት የሕፃናት ጩኸት፤ የአዛውንቶች ሲቃ፤ አቤት ሰይፍ፤ አቤት ቸነፈር፤ አቤት መበተን፤ አቤት ክሳት፤ አቤት መከራና ሰቆቃ!

        የተነሣንበት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ወደ ኤርምያስ ስለ ድርቅ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ አፈሩ . . . ተዋረዱ . . . ራሳቸውንም ተከናነቡ፤ የሚሉትን ቃላት ስናነብ፤ ልክ በዚያ ዘመን እንደ ነበረ ትኩስ ሀዘንተኛ የከበዱብን ነገሮች ወደ ፊታችን ይመጣሉ፡፡ ማንም ሰው በሕይወቱ እንዲህ ያሉ ውርደቶች ባይሆኑ ጽኑ መሻቱ ነው፡፡ ይሁዳ ያለቀሰችበት፤ ደጆችዋም ባዶ የሆኑበት፤ ብርሃኗን የተነጠቀችበት፤ ጩኸቷን አብዝታ ያሰማችበት የጭንቅ ጊዜ፤ የኑሮ በረሃዎቻችንን ግልጥልጥ አድርጎ ያሳየናል፡፡

       እግዚአብሔር የከለከለንን ማንም እንደማይሰጠን፤ የዘላለም አምላክ ያላሰበንን ማንም እንደማያስበን፤ የአማልክት አምላክ ያልራራልንን ማንም እንደማይራራልን፤ የጌቶች ጌታ ያልሰበሰበንን ማንም እንደማይሰበስበን፤ የነገሥታት ንጉሥ ያልሞላውን ጉድለት ማንም እንደማይሞላው፤ እርሱ ከጨከነብን የማንም ፊት እንደማይበራልን የምንረዳበት ክፍል ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ የእግዚአብሔርን ቁጣ በአንድ መንገድ ብቻ እንደምናየው ይሰማኛል፡፡ ከቅጣትና ከጥፋት መልእክቱ አንፃር! ዳሩ ግን እንደዚያ ብቻ መልእክት እንዳለው እንዳናስብ የሚረዱን የእግዚአብሔር ትምህርቶች በቃሉ ውስጥ አሉልን፡፡ በዚሁ በነቢዩ በኤርምያስ የተግሣጽ ክፍል ውስጥ ውሸተኛ ነቢያት በእግዚአብሔር ስም ያልተላኩትን፤ ያላዘዛቸውን፤ ያልተናገራቸውን ግን የልባቸውን ሽንገላ ለሕዝቡ ሲናገሩ እናያለን፡፡ ሰላምን ለሕዝቡ ቢናገሩም፤ በረከትን ለሕዝቡ ቢተነብዩም እንደዚያ ግን አልሆነም፡፡

Tuesday, May 13, 2014

ቀላል ነው!

                                   Please Read in PDF: Kelal New                                                   
                            ማክሰኞ ግንቦት 5 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት  

    ‹‹እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል፡- ነፋስ አታዩም፤ ዝናብም አታዩም፡፡ ይህ ሸለቆ ግን ውኃ ይሞላል፤ እናንተም ከብቶቻችሁም እንስሶቻችሁም ትጠጣላችሁ፡፡ ይህም በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነገር ነው››  (2 ነገ. 3÷17)፡፡

        እግዚአብሔር ከልምምዶቻችን በላይ ነው፡፡ እኛን የሚያጽናናው ራሱን እያጣቀሰ ነው፡፡ እርሱ ብቻ ‹‹እኔ›› ሊል ይቻለዋል፡፡ እኔነት ከእኛ አንፃር ችግር ሲሆን፤ ከእግዚአብሔር አንፃር ግን መፍትሔ ነው፡፡ እኔነት ከእኛ አንፃር ኃጢአት ሲሆን ከእርሱ አንፃር ግን ጽድቅ ነው፡፡ እኔነት ከሥጋ ለባሽ አንፃር ሞት ሲሆን ከጌታ አንፃር ግን ሕይወት ነው፡፡ እኛ ማብራሪያችን ድካምና ብርታት፤ አቀበትና ቁልቁለት ሲሆን እግዚአብሔር ግን ያውና ሕያው ነው፡፡ ያለ፤ የነበረ፤ የሚኖር እንደ እግዚአብሔር ማን ነው? በዓለም ስሌት፤ በሰዎች የአስተሳሰብ ደረጃ፤ በስልጣኔ ክንድ የማይተገበሩ ነገሮችን የእኛ አምላክ ግን ሊያደርግና ሊሠራ ይችላል፡፡ የችግሮቻችን ልዕልና በእኛ ዓይኖች ፊት ብቻ ነው፡፡ በትልቁ እግዚአብሔር ዘንድ የማይቻል የለም፡፡ እግዚአብሔር ‹‹ቀላል ነው›› የሚላችሁ ገምቶ አይደለም፡፡ እርሱ የነገሮችን ጅማሬና ፍፃሜ ጠንቅቆ የሚያውቅ አዋቂ ነውና፡፡ /የሰውን ድካሙን አንተ ታውቃለህ እንዲል ቅዳሴው/

       እኛ ካልገባን፤ ገና ካልተረዳነው ማንነታችን ጋር የምንኖር ምስኪኖች ነን፡፡ ትንሽ ተጉዘን የረጅም የምንፈነጭ፤ ጥቂት ጨብጠን የብዙ የምንፎክር፤ እየተንገዳገድን የቆምን ይመስል፤ እየሸሸን የቅርብ ያህል የሚሰማን፤ እንኳን ከመንፈሳችን ከስሜታችን ጋር የተሸዋወድን፤ ‹‹ያፋልጉኝ›› የተለጠፈበት ሰሌዳ ቢኖር የእኛ እኔነት ነው፡፡ የእግዚአብሔር እጆች እንዲህ ያለውን ሕመምተኛ ማገላበጥ፣ ማጉረስና ቀና ማድረግ፤ ማውጣትና ማግባት ሰልችተው አያውቁም፡፡ ሰው በእግዚአብሔር ቋሚ እንክብካቤ ስር ነው፡፡ የነገሮች ክብደት በእኛ እንደምንኖር ለእኛ የመለፈፋችን ውጤቶች ናቸው፡፡

Saturday, May 10, 2014

አታላምዱን

                                           
                                   Please Read in PDF: Atalamdun

                ቅዳሜ ግንቦት 2 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

       በአንድ አጋጣሚ በአንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ላይ ከሌላ ሁለት ወንድሞች ጋር እየተነጋገርን አሳብ እንለዋወጣለን፡፡ ታዲያ አንደኛው ወንድም አውደ ንባቡ ሊያስተላልፍ ከፈለገው ጠንካራ አሳብና ተግሣጽ ሸሽቶ ያነሠ ነገር ለማንጸባረቅ ሞከረ፡፡ ታዲያ በጊዜው ችላ ብዬ ያለፍኩት ዘግይቶ ግን ያስተዋልኩት ነገር ቢኖር፤ ሰው እግዚአብሔር ካልረዳው በቀር የማይላመደው ነገር አለመኖሩን ነው፡፡ የመጽሐፍ ቅዱሱ ክፍል ክፉ ልምዶችን የሚቃወም ሆኖ ሳለ፤ በጊዜው ግን ወጣቱ እየተላለፈ ያለውን የመለኮት ቃል ቢያውቅም እንኳ ከእግዚአብሔር አሳብ ጋር ለመቆም ፍላጎት አላሳየም፡፡

       እኛ ያልታዘዝነውን ሌሎች እንዳይታዘዙት፤ እኛ ያልደረስንበትን ሌሎች እንዳይደርሱበት፤ እኛ የፈዘዝንበትን ሌሎች እንዳይነቁበት ዝቅታውን ማላመድ ከበደልም በደል ነው፡፡ በየዘመናቱ የእግዚአብሔር ቃል በብዙ ወጀብና አውሎ ውስጥ አልፏል፡፡ ነገር ግን ጎልቶ የማይታይና ቶሎ የማይታወቅ ቢሆንም እንኳ ቃሉን በሚመሰክሩ አገልጋዮች በኩል የሚዘረጋው የጠላት ወጥመድ፤ በተለይ በዘመናችን ለእውነት ተግዳሮት ነው፡፡ ለብዙ ነውሮችና ሃይማኖት ለበስ አመፆች የእግዚአብሔር ቃል እንደ ድጋፍና ሽፋን ሲጠቀስ ማስተዋል እየቀለለ መጥቷል፡፡

Friday, May 2, 2014

ተቤዢዬ ሕያው ነው!

                            Please Read in PDF: Tebeziye Heyaw New
 
                          አርብ ሚያዝያ 24 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት
 
           ‹‹ምነው አሁን ቃሌ ቢጻፍ! ምነው በመጽሐፍ ውስጥ ቢታተም! ምነው በብረት ብዕርና በእርሳስ በዓለቱ ላይ ለዘላለም ቢቀረጽ! እኔን ግን የሚቤዠኝ ሕያው እንደ ሆነ፥ በመጨረሻም ዘመን በምድር ላይ እንዲቆም፥ ይህ ቁርበቴም ከጠፋ በኋላ፥ በዚያን ጊዜ ከሥጋዬ ተለይቼ እግዚአብሔርን እንዳይ አውቃለሁ። እኔ ራሴ አየዋለሁ፥ ዓይኖቼም ይመለከቱታል፥ ከእኔም ሌላ አይደለም። ልቤ በመናፈቅ ዝሎአል።››
(ኢዮ. 19÷23-27)፡፡

           ስለ ቃል ብርታት፤ የሚናገርና የሚሰማ ሁሉ ልብ ይለዋል፡፡ በቃል የቀኑ፤ በቃል የወደቁ፤ በቃል የተጽናኑ፤ በቃል የተሰበሩ፤ በቃል የተሰበሰቡ፤ በቃል የተበተኑ፤ በቃል የጸኑ፤ ቃል ኪዳን ያፈረሱ፤ በቃል ያመለጡ፤ በቃል የተያዙ ምድሪቱ ላይ እንደ ትቢያ ናቸው፡፡ የመጽሐፉ ኢዮብ መልካምንና ክፉን፣ ደስታና ሀዘንን፣ ማግኘትና ማጣትን፣ መክበርና ውርደትን ያየ፤ ሁለቱንም የኑሮ ጽንፍ የነካ ነው፡፡ እንዲህ ያለው ኢዮብ በአሥራ ዘጠነኛው ምዕራፍ ላይ አንዳች እንዲፃፍለት የፈለገውን ቃል በተማጽኖ ጭምር ይነግረናል፡፡ ብዙ ሰው የግል ማስታወሻ ወይም ዲያሪ እንዳለው ልብ እንላለን፡፡ እንደዚህ ያሉ የግል ማስታወሻዎች ዕንባና ፈገግታ፤ መከፋትና ቡርቅታ፤ ተስፋና ሥጋት የሰፈረባቸው ዥንጉርጉር ናቸው፡፡ ለዚህ ጽሑፍ ዝግጅት የተጠና ነገር ለማቅረብ ጊዜው ባይኖረኝም አብዛኛው የጽሑፍ ይዘት መከፋትንና ቅዝቃዜን ማዕከል ያደረገ እንደ ሆነ ይሰማኛል፡፡ በተለይ ለመፃፍ እንደ ሰበብ የሚሆነው ነገር፤ ከሌላው ወደ እኛ የሚመጡ ስብራትና ተስፋ አስቆራጭ ነገሮች ናቸው፡፡

         ኢዮብ ወደዚህ ምድር መምጣቱን የኮነነ፤ የመቃብር ሙቀትን የተመኘ፤ ሥጋውን በጥርሱ ነክሶ ያዘነ፤ በገዛ ወዳጆቹ ግብዝነት የተከበበ፤ ከአምላኩ ጋር ሙግት የገጠመ የመከራ ሰው ነው፡፡ በሕይወቱ ከገጠመው ብርቱ ፈተና የተነሣ የሚናገራቸው እያዳንዱ ቃል በስቃይና ሮሮ የተለወሱ ናቸው፡፡ በመጽሐፉ የተለያዩ ምእራፎች ውስጥ ጠንካራ ጩኸቱንና ያልተቋረጠ ክርክሩን እናነባለን፡፡ እንደዚያ ባለ ስቃይ ውስጥ፤ የወዳጆቹ ፍርደ ገምድልነት፤ የሚስቱ ስንፍና ተጨምሮ ኑዛዜ በሚመስለው ቃሉ ውስጥ ለሥጋ ለባሽ ሁሉ መፍትሔ የሆነ ነገርን ሲናገር ልብ እንላለን፡፡

Thursday, March 20, 2014

የጉብዝና ወራት /ክፍል ሁለት/

                    Please Read in PDF: Yegubzna Werat

                       ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት


     ‹‹ልጆች ሆይ፥ ኃጢአታችሁ ስለ ስሙ ተሰርዮላችኋልና እጽፍላችኋለሁ። አባቶች ሆይ፥ ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ጎበዞች ሆይ፥ ክፉውን አሸንፋችኋልና እጽፍላችኋለሁ።›› (1 ዮሐ. 2÷12-14)፡፡

         መንገድ እየሄድኩ ግርግር ተፈጠረና ፈንጠር ብዬ የሚሆነውን በአንክሮ እከታተል ጀመር፡፡ አንድ ወጣት እጅ ከፍንጅ አንዲት ጉብል ቦርሳ ውስጥ ተገኝቶ ኖሮ የጸጥታ አስከባሪዎች ከብበው ያናዝዙታል፡፡ ታዲያ በተጠየቅ ሂደቱ አንድ የሚያውቀው ሌላ መንገደኛ ድምጹን ከፍ አድርጎ ‹‹እንዴ! እኔ አውቀዋለሁ፡፡ እርሱ ሌባ አይመስለኝም፤ እንዲያውም የሚጥል በሽታ አለበት›› ብሎ መሰከረ፡፡ በዚህ ጊዜ ከጸጥታ አስከባሪዎቹ አንዱ፤ በበሰለ ነገር ላይ ደርሶ አስተያየት ለሰጠው መንገደኛ ‹‹ታዲያ ሴት ቦርሳ ውስጥ ነው እንዴ የሚጥለው?›› ብሎ ሲጠይቅ፤ በዙሪያው የቆመ ሰው ሁሉ ሳቀ፤ አንዳንዱም እኔን ጨምሮ ተሳቀቀ፡፡  

        ዶ/ር ኢዮብ ማሞ ‹‹እይታ /Mindset/›› በሚል መጽሐፋቸው ‹‹ስለምታስበው ነገር ተጠንቀቅ፤ አሳቦችህ ወደ ቃላት ይለወጣሉና፡፡ ስለምትናገረው ነገር ተጠንቀቅ፤ ንግግሮችህ ወደ ተግባር ይለወጣሉና፡፡ ስለምትተገብረው ነገር ተጠንቀቅ፤ ተግባሮችህ ወደ ልማድ (ባህርይ) ይለወጣሉና፡፡ ስለ ልማድህ ተጠንቀቅ፤ ልማድህ የሕይወት ፍፃሜህን ይወስናልና›› (ዶ/ር ኢዮብ ማሞ፤ 2005 ዓ.ም፤ እይታ (Mindset)፤ አዲስ አበባ) በማለት፤ አሳብና አመለካከት በእያንዳንዳችን ሕይወት ላይ ያለውን ጉልህ ተጽእኖ ይናገራሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን አሳብ የያዘ መጽሐፍ ነው፡፡ የፈጠረን አምላክ እንዴት እንድንኖር መመሪያ የሰጠንም በዚሁ ቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡ ሰው አሳቡን፤ ንግግሩን እና ተግባሩን የሚያነፃው በመለኮት አዋጅ ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ቃል ጋር የጠበቀ ግንኙነት ከሌለን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ልንረዳና ልንታዘዘው አንችልም፡፡

Thursday, March 13, 2014

ቤተ ፍቅር

ቤተ ፍቅር መጽሔት ቁጥር ሦስት፡

‹‹ያንብቡ››


Saturday, March 8, 2014

የጉብዝና ወራት /ክፍል አንድ/

                                        Please Read in PDF: yegubzna werat 1
                                                            
      መግቢያ
                          ቅዳሜ የካቲት 29 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

        በአንድ አጋጣሚ ያገኘሁት ከሀገር ውጪ የሚኖር ሰው ስለ ሕይወት እየጠየኩት እንጨዋወታለን፡፡ ምን ዓይነት ውጥረት ውስጥ እያለፈ እንዳለና ከዚህ የተነሣ ትዳር ለመመስረት እንዳልቻለ ከወሬው መካከል ትኩረት ሰጥቶ፤ ስለዚህ ጉዳይ እየደጋገመ በቁጭት ይነግረኛል፡፡ እኔም ኑሮውን ባልካፈለው እንኳ ወሬውን ልጋራው ብዬ እህ . . እህ . . እያልኩ፤ አናቴን እየወዘወዝኩ አደምጣለሁ፡፡ ታዲያ በገረመኝ ሁኔታ በየጨዋታው መሐል ‹‹ተው እንጂ›› ስለው ‹‹ወጣትነቴን አያስጨርሰኝ እልሃለሁ›› እያለ መሐላ ቢጤ ጣል ያደርጋል፡፡ የፀጉሩን ለውጥ፣ የፊቱን ሽብሻብ፣ የወገቡን ጉብጠት፣ የትንፋሹን ቁርጥ ቁርጥ፣ ቢያቀኑት የሚንቋቋ ማጅራቱን፤ የእድሜውን የትየለሌነት እንኳን እኔ፤ በመነጽር ታግዞ የሚመለከትም አዛውንት ልብ እንደሚለው ግልጥ ነው፡፡ ልቤ ‹‹ምን ነካው?›› ለምዶበት ወይስ ያለፈ ናፍቆት ጸንቶበት ይሆን? እላለሁ፡፡ ልቡ ‹‹እስከ ዶቃ ማሠሪያው ንገረው›› አለው መሰል፤ እየደጋገመ ‹‹ወጣትነቴን አያስጨርሰኝ›› ይላል፡፡ እንደ መንደር ሰው ‹‹አይሻልህም ሕፃንነቴን›› ሊለው ሥጋዬ ዳዳ፤ መንፈስ ግን ልጓም ሆነበት፡፡

       እኔን ወንድሜ! አልኩኝ፡፡ ዛሬ ላይ ቆሞ ለትላንት መኖር፣ የያዙት ደብዝዞ ያለፈውን መከጀል፣ የተሸቃቀጠ ኑሮ፣ እድሜን የማያሳይ ድንግዝግዝ፤ ባልንጀራዬ አሳዘነኝ፡፡ እንደሚገባ ያልኖረበት፣ ተላላ ሆኖ ያለፈበት፣ በጭንቅ የሰበሰበውን በፌዝ የበተነበት፣ ምክር ሬት፣ ተግሳጽ ሞት የሆነበትን ለዛሬ መራራ የዳረገውን ወጣትነቱን ትኩር ብዬ ወደኋላ አየሁት፡፡ በኋላ በእንባ የነገረኝን ቀድሜ በመሐላው ደረስኩበት፡፡ ሙከራ ቅኝቱ፣ ስሜት መዘውሩ የነበረውን ወጣትነቱን አወጋኝ፡፡ የሽምግልና እድሜ ሸክም ማቅለያ ሳይሆን፤ ዕዳ ማቆያ የሆነውን የኑሮ እስታይል /ዘይቤ/ እንደሚገለጥ መጽሐፍ አስነበበኝ፡፡ ‹‹ብትችል ሰርዘው፤ ባትችል እለፈው›› እያለ አገላበጠልኝ፡፡ እንባ ያጋቱ ዓይኖቹ፣ የቁጭት ፍም የተከመረባቸው ጉንጮቹ፣ በጥርሱ መጅ የላመ ከንፈሩ፣ ደግፈኝ . . ደግፈኝ የሚለው አፍንጫው፣ በእጆቹ መዳፍ ልምዥግ የሚያደርጋቸው ጢሞቹ፣ የመፍትሔ ያለህ! የሚመታው ልቡ ሁሉም ፊቴ ተራቆተ፡፡

Tuesday, March 4, 2014

ማረፍን ማን ይሰጠኛል?

                                   Please Read in PDF: Marefn man yesetegnal?
                                                    

                              
                                            ማክሰኞ የካቲት 25 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

            ጌታ ሆይ÷ አንተ ታላቅ ነህ÷ ውዳሴም ያለ ገደብ ይገባሃል፤ ኃይልህ ታላቅ÷ ጥበብህም የማይለካ ነው፡፡ የፍጥረትህ ደካማ ክፍል የሆነው የሰው ልጅ÷ ሟችነቱንም ከራሱ ጋር የተሸከመው የሰው ልጅ÷ የኃጢአቱን ምስክርነት÷ የአንተንም የትዕቢተኞችን መቃወም ማስረጃ የተሸከመው የሰው ልጅ÷ አንተን ነው ማወደስ የሚፈልገው፡፡ እንግዲህ ይህ የፍጥረታት ደካማ ክፍል የሆነው የሰው ልጅ ሊያወድስህ ይፈልጋል፡፡

            ‹‹ከጌታ ከራሱ በስተቀር ማን ነው ሌላ ጌታ፤ ወይስ ከእግዚአብሔር ውጭ እግዚአብሔርስ ማን ነው?›› እጅግ ታላቅ፣ እጅጉን የላቀ፣ እጅግ ኃያል፣ እጅግ ሁሉን ቻይ፣ እጅጉን መሐሪ፣ እጅግ ጻድቅ፣ እጅግ የተሰወርክ እጅግ የቀረብክ፣ እጅግ ውብና እጅግ ብርቱ፣ ጽኑና የማትጨበጥ፣ የማትለወጥና ሁሉን የምትለውጥ፣ አዲስ ሆነህ የማታውቅ፣ የማታረጅ፣ ሁሉን የምታድስ፣ እነርሱ ሳያውቁት ትዕቢተኞችን የምታስረጅ፣ ምንጊዜም የምትሠራ፣ ምንጊዜም የምታርፍ፣ የምትሰበስብ፣ ምንም የማያሻህ፣ እየደገፍክ የምትይዝ፣ የምትሞላ፣ የምትከላከልም፣ የምትፈጥር፣ የምትመግብ፣ የምታጠናቅቅ፣ የምትፈልግ፣ ምንም ሳይጎድልህ፡፡

             አንተ ታፈቅራለህ ነገር ግን ያለ ስሜት ነው፤ ቅናትህ መሥጋት የለበትም፡፡ ጸጸትህ ቁጭት አያውቅም፡፡ ቁጣህም የተረጋጋ ነው፡፡ ሥራዎችህን እንጂ እቅድህን አትቀይርም፤ ፈጽሞ ሳይጠፋብህ፤ ያገኘኸውን ትጨብጣለህ፡፡ ምንም ባያሻህም በማግኘትህ ትደሰታለህ፡፡ ስስትን ባታውቅም፤ ብድርን ከነወለዱ ትፈልጋለህ፡፡ ባለእዳ እስክትሆን አብዝተው የሚከፍሉህ፤ ለመሆኑ ያንተ ቢኖረው ካንተ ያልሆነ ሊኖረው የሚችል ማን ነው? ለማንም ባለ እዳ ሳትሆን እዳህን ትከፍላለህ ስትመልስም ምንም አይጎድልብህም፡፡ ኦ አምላኬ ሕይወቴ ቅዱሱ ትፍስሕቴ ሆይ ምን እያልን ይሆን? ስለ አንተ ሲናገር ሰው ምን ማለት ይችላል? ስለ አንተ አብዝተው እንኳን የሚናገሩ እንደ ዲዳ ናቸው - ስለ አንተ የማይናገሩ ወዮላቸው!

Friday, February 21, 2014

ምክር፡

                               
                           አርብ የካቲት 14 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

          ልጄ ሆይ፤ ዋዘኛና ቀልደኛ አትሁን፡፡ በመከራ ለሚኖሩ ሰዎች ሁሉ የምታዝንና የምትራራ ሁን፤ በድኃ ላይ አትጨክን፤ ርስቱንና ቤቱንም በምክንያት አትውሰድበት፤ ለመጨረስም የማትችለውን ነገር አትጀምር፡፡ እሳትና የሞላ ውኃ አትድፈር፡፡ በማናቸውም ነገር ከሚበልጥህ ሰው ጋር ባልንጀርነት አትያዝ፡፡ ከዳኛ ጋር ወዳጅ ሁን፡፡ በፊቱ በቆምህ ጊዜ እውነቱን እንዲፈርድልህ፡፡ ከሀኪምም ጋር ወዳጅ ሁን፡፡ በታመምህ ጊዜ ፈጥኖ እንዲመጣልህ፡፡

          ልጄ ሆይ፤ በልተህ ስትጠግብ ረኃብን፤ ስትበለጥግ ድኅነትን፤ ስትሾም ሽረትን፤ ሌላውንም ይህን የመሰለውን ሁሉ አትርሳ፡፡

         ልጄ ሆይ፤ ለሞተው ወዳጅህ ከማልቀስ ይልቅ በሕይወቱ ሳለ የክፋት ሥራ ለሚሠራ ወዳጅህ አልቅስለት፡፡

         ልጄ ሆይ፤ ባለ ጠጋ ሲወድቅ ሰው ሁሉ ይደግፈዋል፤ ድኃ ሲወድቅ ግን ሰው ሁሉ ወዲያው ይገፋዋል፡፡ ባለ ጠጋ ሲከሰስ በሸንጎ የተቀመጠው ሁሉ ይሟገትለታል፤ ድሀ ሲከሰስ ግን በሸንጎ የተቀመጠው ሁሉ ይፈርድበታል፡፡ መልካም ዳኛ በመካከላቸው የተቀመጠ እንደ ሆነ ግን ፍርዱ እንደ ፀሐይ ያበራለታል፡፡ ስለዚህ በምትኖርበት ሀገር መልካም ዳኛ አያጥፋብህ፡፡

Tuesday, February 18, 2014

ምክር፡

                                    Please Read in PDF: Miker 4

                                       
                    ማክሰኞ የካቲት 11 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

        ልጄ ሆይ፤ ክፉ ሕልም አለምሁ ብለህ አትደንግጥ፡፡ ደግ ሕልምም አየሁ ብለህ ደስ አይበልህ፡፡ ሕልም ማለት የሰው አሳብ እንደ ሆነ እወቅ፡፡ እንኳን ሌሊት በሕልም ቀንም ባይን የታየ ነገር ሳይደረግ ይቀራል፡፡ ደግሞ ሌሊት በሕልም፤ ቀንም ባይን ያልታየ ነገር እንዲያው በድንገት ይደረጋል፡፡ እግዚአብሔር ይሁን ያለው ነገር ጊዜውን ይጠብቃል እንጂ ምንም ቢሆን ሳይሆን አይቀርም፡፡

         ልጄ ሆይ፤ አካልህና ልብስህ ዘወትር ንጹሕ ይሁን፡፡ እጅህን ለሥራ፤ ዓይንህን ለማየት፤ ጆሮህን ለመስማት ፈጣኖች አድርግ፡፡ አፍህን ግን በጠንካራ ልጓም ለጉመህ ያዝ፡፡ አረጋገጥህ በዝግታ፤ አነጋገርህ በለዘብታ ይሁን፡፡ ያልነገሩህን አትስማ፤ ያልሰጡህን አትቀበል፡፡ ያልጠየቁህን አትመልስ፡፡ ሽቅርቅር አትሁን፤ ንብረትህ ጠቅላላ ይሁን፤ ምግብህና መጠጥህ በልክ ሆኖ ያው የጠዳና የጣፈጠ ይሁን፡፡ ምግብህና መጠጥህም የሚቀርብበት ዕቃ ሁሉ ንጹሕ ይሁን፡፡ የምትተኛበት አልጋና የምትቀመጥበት ስፍራ ከእድፍና ከጉድፍ ንጹሕ ይሁን፡፡ በእውነትና በሚገባ ነገር ሁሉ ይሉኝታ አትፍራ፡፡ የምትሠራው ሥራ ሁሉ የመንግሥት ሥራ ካልሆነ በቀር ፖለቲከኛ አትሁን፡፡

Tuesday, February 11, 2014

ምክር፡



                         ማክሰኞ የካቲት 4 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

       ልጄ ሆይ፤ በነገርህ ሁሉ የታመንህ ሁሉ፡፡ በአነጋገርህም ደማም ሁን፡፡ ሰውን የሚያስፈራና የሚያሳዝን ነገር ለመናገር አትድፈር፡፡ በልዝብ ምላስ ሰውን አታታል፡፡ ሰውንም ከሚያሙ ሰዎች ጋር አትደባለቅ፡፡ ልጄ ሆይ፤ ንብረትህ በልክ ይሁን፡፡ ቤተ ሰዎችም አታብዛ የቀንድ ከብትና የጋማ ከብትም በብዙ አታርባ፡፡ ላንተ የማይገባውን ነገር ከማንም ቢሆን አትቀበል፡፡ አንተም ለማንም ቢሆን የማይገባውን ነገር አትስጥ፡፡ የማታገኘውንም ነገር አትመኝ፡፡ በዓይንህ ካላየህና እርግጥ መሆኑን ካልተረዳኸው በቀር በማንም ሰው ላይ የሚወራውን ወሬ እውነት ነው ብለህ አትቀበል፡፡ ለሰውነትህ የሚያስፈልገውን ነገር ለማግኘት አስብ እንጂ ሰው የሚጠፋበትን ሰው የሚጨነቅበትን ነገር አታስብ፡፡

       ልጄ ሆይ፤ ሮጠህ ለማታመልጠው ነገር አትሽሽ፡፡ እርሱም ሞት ነው፡፡ ደጋ ብትወጣ፤ ቆላ ብትወርድ፤ ወንዝ ተሻግረህ ብትሔድ፤ በዋሻ ብትደበቅ፤ ጠመንጃና መድፍ ይዘህ ብትሰለፍ ምንም ቢሆን ከሞት ለማምለጥ አትችልም፡፡ እግዚአብሔርንም ፍራ በሥጋና በነፍስ ላይ ሥልጣን አለውና፡፡ ንጉሥንም አክብር እግዚአብሔር ሠይፍን አስታጥቆታልና፡፡ በአንተም ላይ የሹመት ሥልጣን ያላቸውን አገረ ገዢዎችን ሁሉ አክብራቸው፤ ታዘዝላቸው፡፡ አባትና እናትህን፤ የእግዚአብሔርን ቃል የሚያስተምሩህን መምህሮችህን፤ የሀገር ሽማግሌዎችንና ባልቴቶችን ሁሉ በሚቻልህ ነገር እርዳቸው፡፡

       ልጄ ሆይ፤ ካረጀህ በኋላ እንደ ገና ተመልሼ ምነው ልጅ በሆንኩ ብለህ አትመኝ፡፡ ምንም ቢሆን አታገኘውምና፡፡ ወደፊትም ምነው በሞትኩ ብለህ አትመኝ፤ ምንም ቢሆን አይቀርልህምና፡፡
        ልጄ ሆይ፤ እገሌ ቸር ነው ይበሉኝ ብለህ ገንዘብህን ለማንም አትስጥ፡፡ ለወዳጅ ከመስጠት ለዘመድ መስጠት ይሻላል፡፡ ለጠላት ከመስጠት ለወዳጅ መስጠት ይሻላል፡፡ ከሁሉ ይልቅ ለተቸገሩ ድሆች መስጠት ይበልጣል፡፡ ለድሆች የሰጠ ሰው ብድሩን በሰማይ ያገኛል፡፡

       ልጄ ሆይ፤ ማናቸውንም ነገር ቢሆን ለመስማት እንጂ ለመናገር አትቸኩል፡፡ ከወዳጅህም ጋር በተጣላህ ጊዜ ቀድሞ በወዳጅነታችሁ ጊዜ የነገረህን ምስጢር አታውጣበት፡፡ ከወዳጅህም ጋራ አንድ ጊዜ ጠብ ከጀመርክ በኋላ፤ ምንም ብትታረቅ ሁለተኛ ምስጢርህን ለእርሱ ለመናገር አትድፈር፡፡ ቂምህንም አትርሳ፡፡ ቂምህን አትርሳ ማለቴ ከታረቅህ በኋላ ክፉ አድርግበት ማለቴ አይደለም፡፡ ነገር ግን እርሱ ሞትንና ኩነኔን የማያስብ ክፉ ሰው የሆነ እንደ ሆነ እርቅ አፍርሶ እንዳያጠፋህ ሳትዘናጋ ተጠንቅቀህ ተቀመጥ ማለቴ ነው፡፡

Sunday, February 9, 2014

ምክር፡

                                   Please Read in PDF: Miker 2                                 
                                 
                           እሁድ የካቲት 2 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት


       ልጄ ሆይ፤ ይህ ዓለም ቀድሞ ከወዴት መጣ ኋላስ ወዴት ይሄዳል ብለህ ለመመርመር አትጨነቅ፡፡ እንኳን የዓለምን ነገር የራስህንም ነገር መርምረህ ለማወቅ አትችልም፡፡ አሳብህም ሁሉ ለዛሬ ብቻ ይሁን እንጂ ላለፈው ቀን ለትናቱ፤ ወይም ለሚመጣው ቀን ለነገ አታስብ፡፡

      ልጄ ሆይ፤ ወዳጅ ማለት ሰው አይምሰልህ፡፡ ነገር ግን ወዳጅ ማለት ጊዜ ነውና በጊዜህ ሁሉ ይወድሃል፤ አለጊዜህ ግን ወዳጅህ እንኳ ይጠላሃል፡፡ ጊዜ ማለትም ቀንና ሌሊት አይምሰልህ፡፡ ነገር ግን ጊዜ ማለት የእግዚአብሔር አሳብ የሚፈጸምበት ነው፡፡ ስለዚህ በሆነውም በሚሆነውም ነገር ሁሉ የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን እያልህ ተቀመጥ፡፡

      ልጄ ሆይ፤ ብዙ ተድላና ደስታ ለማድረግ አትጨነቅ፤ ይህንን ለማድረግ የፈለግህ እንደ ሆነ ግን ለሰው መራራትና ደግነትን አታገኛቸውም፡፡ ስለዚህ ተድላና ደስታህ በልክ ይሁን፤ እድሜህንም ያለ ሀዘንና ያለ መከራ በደስታ ብቻ ለመጨረስ አይሆንልህም፡፡ ነገር ግን ሀዘንና ደስታ ከባሕርይህ ጋር ባንድነት ተዋህደው የሚኖሩ ናቸውና በእድሜህ ሙሉ ሁለቱንም በየተራ ታገኛቸዋለህ፤ ካልሞትህም በቀር ከኀዘንና ኃጢአት ከመሥራት አትድንም፡፡

      ልጄ ሆይ፤ መቅሰፍት ይመጣብኛል ብለህ አትጨነቅ፡፡ ትልቅ መቅሠፍት ማለት አሳብ ማብዛት ነው፡፡ ልጄ ሆይ፤ የሰውን ነገር ችሎ ለማይኖርና አሳብ ለሚያበዛ ከኃጢአቱም ለማይመለስ ሰው ቶሎ መሞት ይሻለዋል፡፡

      ልጄ ሆይ፤ ደጉን ሰው ለማጥፋት አታስብ፤ ደጉን ሰው ለማጥፋት ብታስብ ግን ራስህን ጨምረህ ታጠፋለህ፡፡ ለሌላ ሰውም የክፋትን መንገድ አታስተምር፡፡ ፈጣሪህም እግዚአብሔር እንደ ሆነ እመን፡፡ ነገር ግን የእርሱን መጀመሪያና መጨረሻ መርምሬ አገኘዋለሁ ብለህ አትጨነቅ፡፡

Friday, February 7, 2014

ምክር፡

                         አርብ ጥር 30 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

       ‹‹የተወደድህ ልጄ ሆይ፤ ሰው ሁሉ በዚህ ዓለም የሚኖርበት ዘመኑ እጅግ አጭር ነው፡፡ ከዚያም የሚበዛው በመከራና በሀዘን ይፈጸማል፡፡ ይህንንም መከራና ሀዘን አንዳንድ ሰዎች በገዛ እጃቸው ፈልገው ያመጡታል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን ሳያስቡት በድንገት ይመጣባቸዋል፡፡ መከራና ሀዘን በገዛ እጃቸው ፈልገው የሚያመጡ እንዴት ያሉ ሰዎች ናቸው ትለኝ እንደ ሆነ ስማኝ ልንገርህ፡፡

       አንዳንድ ሰዎች የሰው ገንዘብ ሊሰርቁ ሄደው እዚያው ይሞታሉ ወይም ተይዘው ይቀጣሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች የሰው ሚስት ለመቀማት ሄደው እዚያው ላይ ይሞታሉ ወይም ይቆስላሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ሰውን ለማጥፋት የሐሰት ነገር ይዘው ይነሡና ባወጡት ዳኛ በቆጠሩት ምስክር ተረተው ይቀጣሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች የሰው ማኅተም አስመስለው ቀርጸው አትመው በውስጡም የሐሰት ቃል ጽፈው ይገኙና ይቀጣሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች አይታወቅብንም አይሰማብንም ብለው ንጉሥ ለመግደል  መንግሥት ለማጥፋት ሲመክሩ ይገኛሉና ብርቱ ቅጣት ይቀጣሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ለኩራትና ለትእቢት ብለው አንበሳና ዝሆን ለመግደል በረሃ ይወርዱና በበረሃ በሽታ ይሞታሉ ወይም ያው ለመግደል የፈለጉት አውሬ ይገድላቸዋል፡፡

       እነዚህን የመሰሉ በገዛ እጃቸው መከራንና ኀዘንን በራሳቸው የሚያመጡ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ደግሞ ሳያስቡት በድንገት መከራና ኀዘን የሚመጣባቸው እንዴት ያሉ ሰዎች ናቸው ትለኝ እንደ ሆነ ስማኝ ልንገርህ፡፡

Wednesday, February 5, 2014

ከዛፉ ውረዱ (ካለፈው የቀጠለ)


                                 Please Read in PDF: Kezafu Weredu 2
                                                                     
                           እሮብ ጥር 28 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

            ሱሰኛ መሆን ማለት፡

1. በአንድ ነገር ተጽእኖ (ባሪያ) ስር ማደር ነው፡ ሰዉ በቤተሰቡ አልያም ራሱን በራሱ የሚያስተዳድር ብቻ አይደለም፡፡ የተለያዩ አሳዳሪዎችም አሉት፡፡ ከአንዳንዶቹ ለመፈታት ጥቂት አቅም የሚጠይቅ ሲሆን ሌሎቹ ግን በአብዛኛው ያታግላሉ፡፡ ሱስ ባሪያ ላደረገን ነገር መኖር ነው፡፡ በማያቋርጥ ድግምግሞሽ ከተሸነፍንለት ሱስ ጋር መታየት ነው፡፡ አንድ ሰው ያለ ተጨማሪ ነገር ሊከውን የሚችለውን ያለ ሱሳችን ማድረግ አለመቻልም ነው፡፡ ተጽእኖው ያየለ እንደ መሆኑ ሕይወትን እስከ መክሰር ወዳሉ ውሳኔዎች ያደርሳል፡፡ ለአመጽ ያስጨክናል፣ ለጭብጥ እፍኝ  የማይሞላውን ያደፋፍራል፡፡ ከእውነታው ጋር ሳይሆን ከምናባችን ጋር ነዋሪ ያደርገናል፡፡ ማኅበረሰቡ ትልቅ ግምት ለሚሰጣቸው ነገሮች ትኩረት ነፋጊ መሆንን ያስከትላል፡፡ በጋራ እንድንኖርባት በተሰጠችን ዓለም የራሳችንን ሌላ ዓለም እንድንፈጥርና ራሳችንን እንድናገልል እንሆናለን፡፡ ‹‹አላስችልህ አለኝ›› የምንልበት ጎጂ ነገር ካለ በእርግጥም ሱሰኛ ሆነናል ማለት ነው፡፡

        አብዛኛውን ጊዜ ሱስን ከጫት፣ ከሲጋራ፣ ከሀሺሽ፣ ከአልኮል . . ጋር ብቻ ማያያዝ የተለመደ ነው፡፡ በእርግጥ እንደነዚህ ያሉ ነገሮች በግልጥ የምናስተውላቸውና ማኅበረሰቡ ችግሩ መሐል ሆኖ ሲቃወማቸው የቆዩ ጎጂ ልምምዶች ናቸው፡፡ ነገር ግን ጠንከር ያለና ቁርጥ ተቃውሞ ታይቷል ለማለት አያስደፍርም፡፡ እኔ እንደማስበው ለዚህ ምክንያቱ ማኅበረሰቡ ከፍተኛ ግምት የሚሰጣቸው ሰዎች ራሳቸው ሱሰኛ መሆናቸው ይመስለኛል፡፡

       በሱሰኝነት ላይ የተደረጉ ጥናቶችን በተወሰነ መልኩ ለማየት ሞክሬያለሁ፡፡ ዳሩ ግን ተግባራዊ ለመሆንና ለውጥ ለማምጣት አልታደሉም፡፡ ምናልባትም ጥናቶቹ ራሳቸው በሱሰኞች የተሠሩ ይመስሉኛል፡፡ ያልተለወጠ አይለውጥምና ቤተ መፃሕፍት ከማሞቅ ያለፈ ወደ ሞት እሳት እየተማገደ ያለውን ትውልድ ሊታደጉት አልቻሉም፡፡ ሱሰኝነት ከተለያዩ አመሎች ጋር ይዛመዳል፡፡ ጫት ማላመጥ ብቻ ሳይሆን ክፋት ማመንዠግም ሱስ ሆኖ ይታያል፡፡ ሲጋራ ማጨስ ብቻ ሳይሆን ሰው ማጨስም ከባድና ጎጂ ሱስ ነው፡፡ ‹‹አመሏ ነው›› እንደ ልባቸው እንዲኖሩ ፈቃድ የሆናቸው ብዙ ሱሰኞች አሉ፡፡ የተላመድነው ክፉ ጠባይ ካላስገበረ ያስፋሽካል፡፡   

Sunday, January 19, 2014

ልዩ፡ በመለኮት ጃን ሜዳ

                                       Pleas Read in PDF: Yemelekot Janmeda
                                                                     
      ‹‹የዚያን ጊዜ እኔ በእርሱ ዘንድ ዋና ሠራተኛ ነበርሁ ዕለት ዕለት ደስ አሰኘው ነበርሁ፥ በፊቱም ሁልጊዜ ደስ ይለኝ ነበርሁ፥ ደስታዬም በምድሩ ተድላዬም በሰው ልጆች ነበረ።›› (ምሳ. 8፥30-31)፡፡

       ቅዱሳት መጻሕፍት የዘላለም አባት፣ የዘላለም ልጅ እና የዘላለም መንፈስ እንዲሁም የዘላለም አሳብ እንዳለ በግልጥ ይናገራሉ (ዘዳ. 33፥27፣ ዮሐ. 1፥1-2፣ ዕብ. 9፥14፣ ኤፌ. 3፥11)፡፡ ፍጥረት በመለኮት ጉባኤ ውሳኔ ወደ ሕልውና ሳይመጣ፣ ሰው በእግዚአብሔር መልክና ምሳሌ ሳይሆን፣ ሰማያትና ምድር ሳይከናወኑ፣ ከዘመን መቆጠር አስቀድሞ ባልተፈጠሩ ሰማያት፣ ባልተቆጠሩ ዘመናት የአብ፣ የወልድና የመንፈስ ቅዱስን አኗኗር ስንመለከት በአካል ሦስትነት የባሕርይ አንድነታቸውን እናስተውላለን፡፡ ሦስት አካላት የሚደሰቱበት አንድ የመለኮት ደስታ ወደ ሕሊናችን ይመጣል፡፡ በጉባኤው መካከል የእርስ በእርስ ተድላቸውንም ልብ እንላለን፡፡  

      አባት በልጁ ደስ ሲሰኝ ልጅም በዚያው ልክ ያለመቀዳደምና መበላለጥ በአባቱ ደስ ይሰኛል፡፡ መንፈስ ቅዱስም እንዲሁ፡፡ ሕብረትን የሚሻ እግዚአብሔር ከፍቅሩ የተነሣ ደስታው በምድሩ፣ ተድላውም በሰው ልጆች መካከል እንዲሆን ወደደ፡፡ እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ (ዘፍ. 1÷26)። ሰው እግዚአብሔር ያሰበለት አሳቡ፣ ያየለት ዕይታው፣ ያዘዘው ኑሮው አልሆን ብሎት ባለመታዘዝ አምላኩን በደለ፡፡ ጥንቱንም በምክሩ ቢበድል አድነዋለሁ፡፡ ለኃጢአቱም ቤዛ እከፍላለሁ ያለ ፈጣሪ ለሰው የመዳንን ተስፋ በበደለበት ሥፍራ ነገረው፡፡ እግዚአብሔር በመልኩ እንደ ምሳሌው የፈጠረው ሰው በመልኩ እንደ ምሳሌው ኃጢአተኛ እየወለደ ሁሉ ኃጢአትን ሰርተዋል ተባለ (ሮሜ. 3)፡፡ የእግዚአብሔርም ክብር እንደ ጎደለን የጎደለን እግዚአብሔር ነገረን፡፡

       የእግዚአብሔር ልጅ በሥጋ ተገለጠ፡፡ በመለኮት አስቀድሞ ማወቅ ለታየው የሰው በደል ‹‹እኔ ቤዛ እሆናለው›› ያለው ወልድ ከድንግል ተወለደ፡፡ የዚህችም ድንግል ስሟ ማርያም ነው፡፡ ‹‹ኮነ ወልደ እጓለ እመሕያው ዘበአማን ወውእቱ ፍኖት ዘይመርሀነ ኀበ አቡሁ ቅዱስ /እርሱም በእውነት ሰው የሆነ ወደ ቅዱስ አባቱ የሚመራን መንገድ ነው/››፡፡ በዘላለማዊ ልደት የአብ የዘላለም ልጅ የእግዚአብሔር ቃል ወልድ የሰው ጠባይዕ የሆኑትን ነፍስን ሥጋን መንፈስን ተገንዝቦ ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እኛን መሰለ፡፡ እኛም ፍጹማንና ምሉዓን የሆኑት መለኮቱና ሰውነቱ የባሕርይ መደባለቅና መለወጥ የአቅዋም ሽረትና ፍልሰት ሳይኖርባቸው ጭራሹን ያለመለየትና ያለመከፈል በአንዱ የአካል ተዋሕዶ አንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን እናምናለን፡፡

Thursday, January 16, 2014

ከዛፉ ውረዱ


                                  Please Read in PDF: Kezafu Weredu


                     
                                         ሐሙስ ጥር 8/ 2006 የምሕረት ዓመት

        ለአገልግሎት ወደ አንድ ከተማ ሄጄ ካሰብኩበት ቦታ እንዲያደርሰኝ በፈረስ ተጎታች ጋሪ ላይ ተሳፈርኩ፡፡ እስቲ እኔም ወግ ይድረሰኝ፣ ኮንትራት ልያዝ ብዬ ሙሉ ሂሳቡን ልከፍለው ተስማምቼ መንገድ ቀጠልን፡፡ ትንሽ በሄድን ቁጥር ሾፌሬን ሰዎች በተደጋጋሚ ሰላምታ ይሰጡታል፡፡ ታዲያ ማን ብለው እየጠሩ መሰላችሁ ‹‹ዶክተር›› በጣም ተገርሜ ‹‹ያሉት እውነት ነው?›› ብዬ ጠየኩት፡፡ እርሱ ግን እየሳቀ ‹‹ቆጥረውኝ ነው›› አለኝ፡፡ እኛ ማኅበረሰብ ውስጥ እየተቆጠረላቸው ከሆኑት በላቀ፣ ከጨበጡት ባለፈ የሚታሰቡ ብዙ ሰዎችን አስተውያለሁ፡፡ ይህ ግን አግራሞቴን አገሸበው፡፡ ሰዉ ለዓመታት ቀን ከሌሊት ደክሞ የሚደርስበትን ሙያ እርሱ እያፌዘ ሲጠራበት ተደነኩ፡፡ በሙያ ስሞች የሚደረጉ ማጭበርበሮችን ሰምቻለሁ፡፡ ቢያንስ እንደዚህ የሚጠራው ጋሪ ነጂ (ዶ/ር) ማኅበረሰቡን ልብላው፣ ላጭበርብረው፣ ላምታታው፣ ቀን ልውጣበት ብሎ አለመነሣቱ፤ ያለውን ኑሮ ተቀብሎ ለሥራ መልፋቱ በልቤ መደነቅ፣ ከንፈሬ ላይ አግራሞት፣ ኮንትራቱ ላይ ደግሞ ተጨማሪ አንድ ብር አስገኘለት፡፡

        መንደሮቹን ስናሳብር ‹‹ዶክተሬ›› ብላ አንዲት መልከ መልካም ሸንቃጣ ወጣት ‹‹ስትመለስ›› አይነት እጇን አወዛወዘች፡፡ ደግሞ እሷን ‹‹ምኗን አክመሃት ነው?›› አልኩት፡፡ እንደ ማፈር ሲል ‹‹ግድ የለም ንገረኝ ያለው ጋሪና ፈረሱ ነው፡፡ ይታዘበኛል ካልክ ያለ ሰው ምስክር እኔን ነው›› ብዬ አደፋፈርኩት፡፡ ከጠየከኝማ ብሎ ነው መሰል ያስነወራቸውን፣ ሲያልፍም ልጅ ያስወለዳቸውን፣ እንደ ሕመምተኛ ተቅለስልሰው የቀረቡትንና የፈወሳቸውን (በሱ ቤት) ዘረዘረልኝ፡፡ እጅብ ያለ ማሳ የመሰለ ጠጉሩን፣ በሻርብ የተጠቀለለ ፊቱን፣ አቧራ የተኳለ ዓይኑን አፍጥጬ አየሁት፡፡ እሺ! ዶክተር በሚል ስሜት ራሴን ወዘወዝኩለት፡፡ ብዙ እንደ ሰማሁ የማልጽፈውን ቀዶ ጥገና ነገረኝ፡፡ በገባው ላናግረው ብዬ ‹‹ለመሆኑ የካርድ ይከፍላሉ›› አልኩት፡፡ ተያይተን ተሳሳቅን፡፡

Tuesday, January 7, 2014

እንኳን አልደረሳችሁ

                        Please Read in PDF: Enkuan Alderesachw

                             ታህሳስ 29 ቀን 2006 የምሕረት ዓመት

         ከሚታየው በሌላኛው ጎን መመልከት፣ ግዙፉን አልፎ ረቂቁን ማስተዋል ከበዓላቶቼ መካከል አንዱ ነው፡፡ ቃሉም ‹‹የሚታየው የጊዜው ነውና የማይታየው ግን የዘላለም ነው›› (2 ቆሮ. 4÷17) ይለናል፡፡ ሰዎች በተስማሙባቸው የተለዩ ቀናቶች ውስጥ ደስታ ብቻ ሳይሆን ሀዘን፣ እረፍት ብቻ ሳይሆን ሁከት፣ ሰላም ብቻ ሳይሆን ክርክርም ይስተዋላል፡፡ የመመገብ ሽር ጉድ እንዳለ ሁሉ ያለመብላት ፍላጎት፣ የመንቀሳቀስና ወዳጅ ዘመድን የመጠየቅ ዝንባሌ እንደሚስተዋል ሁሉ እግርና እጅን አጣጥፎ ከቤት ያለመውጣት ሲያልፍም የመተኛት ሁኔታ ይታያል፡፡ ሰዎች ሁሉ እንደዚህ ያሉት ቀናት የደስታ እንደሆኑ ቢስማሙም እንኳ ሁሉ ግን አይደሰትም፡፡

          ለዚህ ርእሰ ጉዳይ መነሻ የሆነኝ ከተወሰኑ ዓመታት በፊት ለአገልግሎት ሄጄ ቤታቸውን ማረፊያ አድርገው በእንግድነት በተቀበሉኝ ቤተሰቦች ዘንድ ያስተዋልኩት አሳዛኝ ታሪክ ነው፡፡ እማወራዋ ከተቀመጡበት ለመነሣት፣ ከሰው ጋር ብዙ ለማውራት፣ የቀረበላቸውን ምግብ ለመብላት አቅሙም ሆነ ፍላጎቱ የላቸውም፡፡ አብዝቶ መተከዝ፣ ሲያልፍም ማንባት፣ ብቻ መቀመጥ፣ ስልቹነት የቀን ውሏቸው ነው፡፡ የልጆች ከበባ፣ የአባወራው ቁልምጫ፣ የእኛ የእንግዶቹ ማባበያ የሀዘናቸውን ክምር፣ የትካዜያቸውን ቁልል አልፎ ሊዘልቅ አልቻለም፡፡ አልፎ አልፎ ከሚቀምሱት ምግብ ውጪ ቀለባቸው መቆዘም ነው፡፡

        ለዚህ የዳረጋቸው የበዓልን ዋዜማ ለሥራ ወጥቶ፣ ከሽፍቶች በተተኮሰ ጥይት ጭንቅላቱን የተመታ ሬሳ (ልጃቸው) በዚያው ምሽት መኖሪያ ቤታቸው ድረስ መጥቶላቸው ነው፡፡ ከዚያን ቀን ጀምሮ ለእርሳቸው በዓል የሚባል ነገር ትርጉም አይሰጣቸውም፡፡ እርሳቸውን ‹‹እንኳን አደረሰዎ›› ማለት ለትካዜ ርእስ መስጠት፣ ላለፈ ሀዘናቸው ግርሻት መሆን ነው፡፡ እንደ ትኩስ ሬሳ ብቸኛ ወንድ ልጃቸውን ስላጡበት ክፉ አጋጣሚ ይተርኩላችኋል፡፡ ዓመታት ቢያልፉም እርሳቸው መቃብሩ ስር ያሉ ያህል በአሳብ ያምጣሉ፡፡ አለማልቀስ እርሳቸው ፊት አይቻልም፡፡ እንኳን ዕንባ ከዓይናቸው ፈስሶ ፍም የሚመስለው ፊታቸውንም ማየት ለወዮታ ይጋብዛል፡፡ ከብዙ ዓመታት በኋላም ፊቴ ላይ ድቅን ይሉብኛል፡፡