Monday, February 23, 2015

መጽሐፍ ቅዱስ ለማጥናት የሚሆን ምክር፡


ሰኞ የካቲት 16 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት
1.    መጽሐፍ ቅዱስን በየቀኑ አጥና፡፡ 
መጽሐፍ ቅዱስን ሳያስታጉሉ ማጥናት ትልቅ በረከት ነው።
/ እንጀራ የሥጋ ምግብ እንደሆነ የእግዚአብሔር ቃልም የመንፈስ ምግብ ነውና። «ሰው በእንጀራ ብቻ ሊኖር አይቻልም ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣው ቃል ሁሉ እንጂ።›› (ማቴዎስ፡44)፤ ‹‹ለሚጠፋ መብል አትድከሙ፤ ለዘለዓለም ለሚኖረው ምግብ (መብል) እንጂ›› (ዮሐ.627)፡፡
/ ማጥናትን አንድ ቀን የተውህ እንደሆነ ፈጽሞ ለመተው ልምድ ምናልባት ይሆንብሃልና።
/ ምግብ ለሰውነት አስፈላጊ እንደሆነ እንዲሁም ዘወትር መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት ለመንፈሳዊ ሕይወት አስፈላጊ ነው። ሙዋቹ የእንግሊዝ ንጉሥ ጆርጅ 5 ማናቸውም ሥራ ቢኖርባቸው መጽሐፍ ቅዱስን በየቀኑ ያነቡ ነበር ይባላል። ጆን ክሪዞስቶም በሌሎች ቅዱሳት መጻሕፍት በየቀኑ ከሚያጠኑት በላይ የሮሜን መልእክት በሳምንት ሁለት ጊዜ ያነቡት ነበር። በየቀኑ 20 ምዕራፍ የሚያነብ አንድ ወዳጅ አለኝ፡፡ በየቀኑ ብዙ ምዕራፍ ማጥናት አስፈላጊ አይደለም። ነገር ግን ጥዋት አንድ ምዕራፍ ወይም የምዕራፍ አንድ ክፍል ቢቻልም ማታ ሌላ ምዕራፍ ማጥናት አስፈላጊ ነው።

Thursday, February 19, 2015

የጽድቅ መንገድ

                                             

                         በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
                                 ሐሙስ የካቲት 12 ቀን 2007 ምሕረት ዓመት
         ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም ከመምጣቱ አስቀድሞ እውነተኛ የጽድቅ መንገድ አልታወቀም ነበር። ነገር ግን ዛሬ ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር እውነተኛውን የጽድቅ መንገድ አሳየን። ይኸውም የጽድቅ መንገድ የተባለ አንድ ልጁ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ከሱ በቀር ሌላ ወደ ሰማያዊ አባታችን ወደ እግዚአብሔር የሚወስድ የለም። እርሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኔ የእውነትና የሕይወት መንገድ ነኝ በኔ በኩል ካልሆነ በቀር አንድም ወደ አብ የሚመጣ የለም ብሎ ተናግሮዋል። (ዮሐ. 146)፡፡

Saturday, February 14, 2015

ተቆራረጥን

                                                                     

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አርብ የካቲት 6 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

      ከተወሰኑ ዓመታት በፊት አንድ አጋጣሚ በዚህ ሰሞን ትዝ ይለኛል፡፡ ስልክ ተደውሎ መልእክት እንዳለኝ ተነገረኝ፡፡ መልእክቱ ከማን እንደመጣ፤ ምን እንደ ሆነ ለመጠየቅ ያደረኩት ሙከራ፤ እኔን ለማስደነቅ ሊደረግ ባለ አሳብ ምክንያት ዘገየ፡፡ ይህንንም ‹‹ይቆይህ›› ብለው አሳሰቡኝ፡፡ እኔም ለጊዜው ካላወኩት ሰው የመጣውን መልእክት ለመቀበል አመነታሁ፡፡ ዳሩ ግን የተላኩት ሰዎች ዋጋ ተቀብለውበታልና ጠንከር ባለ ቃል ጭምር የት እንዳለሁ ደጋግመው ጠየቁኝ፡፡

      ሽጉጥም ቢሆን አደባባይ ላይ ይሻላል ብዬ ፒያሳ ከምን ይልክ ሐውልት ዝቅ ብሎ ባለው አካባቢ ፀሐይ እየሞኩ፤ መጽሐፍ ገልጬ ቀጠርኳቸው፡፡ ቀጥሎ ምን እንደ ሆነ ለመናገር ትንፋሽ እንድሰበስብ ፍቀዱልኝ . . . መልእክተኞቹ አካባቢው ላይ ደርሰው በስልክ ልብስና መልኬን ጠየቁኝ፡፡ እግዚአብሔር አያድርስባችሁ፤ ሁለት ቁመታቸው ዘለግ፤ ደረታቸው ሰፋ፤ ጡንቻቸው ፈርጠም ያሉ ወጣቶች በፍጥነት ወደ እኔ እየተራመዱ መጡ፡፡

Monday, February 9, 2015

ያዘጋጃል

                             በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

  ሰኞ የካቲት 2 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

        ‹‹እግዚአብሔርም ሳሙኤልን፦ በእስራኤል ላይ እንዳይነግሥ ለናቅሁት ለሳኦል የምታለቅስለት እስከ መቼ ነው? በቀንድህ ዘይቱን ሞልተህ ሂድ በልጆቹ መካከል ንጉሥ አዘጋጅቻለሁና ወደ እሴይ ወደ ቤተልሔም እልክሃለሁ አለው።›› /1 ሳሙ 16÷1/!

        ‹‹. . . ሁሉን ያዘጋጀ ግን እግዚአብሔር ነው›› /ዕብ. 3÷4/፤ በብዙዎቻችን ልብ ውስጥ ዕረፍት እንዲሰማን ከሚያደርጉ የእግዚአብሔር አሳቦች መሀል አንዱ ነው፡፡ ብዙ ወገኖች ለድግሳቸው ማጀቢያ ጥቅሱን ይጠቀሙታል፡፡ ዳሩ ግን በሰው ዝግጅት ውስጥ የምናወጣቸው ብዙ እንከኖች ይኖራሉ፡፡ ሰው የቻለውን ያህል ተዘጋጅቶ ገና አሁንም የዝግጅት እጥረት እንዳለበት ልናወራ እንችላለን፡፡

        ሙሉ ያልነው ጎድሎ፤ ረጅም ያልነው አጥሮ፤ መልካም ያልነው ከፍቶ፤ ጉልህ ያልነው ደብዝዞ፤ ይበቃል ያልነው አንሶ እንቸገራለን፡፡ የሁሉም ዓይን ተስፋ በሚያደርገው /መዝ. 144፤15/ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ፈጽሞ እንዲህ የለም፡፡ እርሱ እግዚአብሔር የሚያስፈልገንን ሳንጠይቀው ቀድሞ ያውቃል፤ ከመሻታችንም አልፎ ሁሉን ያዘጋጃል /ማቴ. 6፡32/፡፡