Monday, May 30, 2016

መልእክት ፡ ኀበ ፡ ሰብአ ፡ ኤፌሶን፡፡ (2)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!



የሐዋርያው ፡ የጳውሎስ ፡ መልእክት ፡ ወደ ፡ ኤፌሶን ፡ ሰዎች፡፡

ሰኞ ግንቦት 22 ቀን 2008 የምሕረት ዓመት

‹‹ወአርአየነ ምክረ ፈቃዱ በከመ ሥምረቱ›› (ኤፌ. 1፡9)!

v  የጥናቱ መግቢያ

·  የኤፌሶን ቤተ፡ ክርስቲያን የተመሰረተችው በሐዋርያው ጳውሎስ ሁለተኛ ሐዋርያዊ የአገልግሎት ጉዞ ነው፡፡

·  ሐዋርያው በቆሮንቶስ ከተማ ለ18 ወራት ከነበረው የአገልግሎት ቆይታ በኋላ (ሐዋ. 18፡11)፤ ከጵርስቅላና ከአቂላ ጋር በመሆን ኤፌሶንን ጎብኝቷል (ሐዋ. 18፡18)፡፡

·  ሐዋርያው በኤፌሶን የነበረው የመጀመሪያ ቆይታ ለአጭር ጊዜ የነበረ ሲሆን፤ ዳሩ ግን እንደሚመለስ ቃል ገብቶላቸው ነበር (ሐዋ. 18፡19-21)፡፡ ነገር አዋቂ፤ በመጻሕፍት እውቀት የበረታ፤ የጌታን መንገድ የተማረ፤ የዮሐንስን ጥምቀት የሚያውቅ፤ በመንፈስ የሚቃጠል፤ ስለ ኢየሱስ የሚናገርና በትክክል የሚያስተምር ለሆነው አጵሎስ ‹‹የእግዚአብሔርን መንገድ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት›› የተባለላቸው ጵርስቅላና አቂላ በኤፌሶን ቆይተዋል (ሐዋ. 18፡24-26)፡፡

· ሐዋርያው በሦስተኛ ሐዋርያዊ ጉዞው ወደ ኤፌሶን የተመለሰ ሲሆን፤ በዚያም ለሦስት ዓመታት በአገልግሎት ቆይቶአል (ሐዋ. 19፡8-10፤ 20፡31)፡፡ አንደኛ እና ሁለተኛ የቆሮንቶስ መልእክታትን የጻፈው በእስያ ዋና ከተማ ከሆነችው ከኤፌሶን ነው (1 ቆሮ. 16፡8፤9)፡፡ በዚያ ብዙ ድንቅና ተአምራት በእርሱ በኩል ተከናውነዋል (ሐዋ. 19፡12)፡፡

· ሐዋርያው በእድሜው ማብቂያ ከኤፌሶን አስጠርቶአቸው ከመጡ ሽማግሌዎች (ባለ አደራ) ጋር በሚሊጢን እንደተገናኘ፤ ምክርና ማስጠንቀቂያ አዘል የስንብት መልእክት አስተላልፏል (ሐዋ. 20፡16-38)፡፡

Tuesday, May 3, 2016

ምስኪን ማነው?

             በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
             

ማክሰኞ ሚያዝያ 25 ቀን 2005 የምሕረት ዓመት


         በክርስትና መሠረተ ትምህርት ውስጥ የ‹‹ትንሣኤ ሙታን›› አሳብ በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡  ሐዋርያው ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የመጀመሪያይቱን የቆሮንቶስ መልእክት ሲጽፍ በጊዜው መፍትሔ ከተሰጠባቸው ችግሮች አንዱ ‹‹ትንሣኤ ሙታን የለም›› የሚለው የአንዳንድ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች መረዳት ነው፡፡ የቆሮንቶስ መልእክት በምሕረቱ ባለ ጠጋ (ኤፌ. 2፡4) የሆነውን የእግዚአብሔርን ጸጋ የምናስተውልበት መጽሐፍ ነው፡፡ በመልእክቱ መግቢያ ‹‹በቆሮንቶስ ላለች ለእግዚአብሔር ቤተ፡ ክርስቲያን፤ በክርስቶስ ኢየሱስ ለተቀደሱት›› (1፡2) የሚለው አገላለጽ እግዚአብሔር በክርስቶስ ያሉትን ምእመናን ድካም የሚመለከትበትን የጸጋ ዓይን እንድናይ ያደርገናል፡፡

ምእራፍ 15፡ 
ርዕስ፡ - ትንሣኤ እርግጥ ነው!

                       .  የክርስቶስ ትንሣኤ ወንጌል (1-11)
                       .  ክርስቶስ ባይነሣ ስፍራችን (12-19)
                       .  ክርስቶስ እንደ በኩራት (20-28)
                       .  ስለ ሙታን ትንሣኤ የቀረበ ተግባራዊ ማስረጃ (29-34)
                       .  ስለ አካል መነሣት የተሰጠ ትምህርት (35-49)
                       .  የጌታ መምጣትና በእርሱ በኩል ያለን ድል መንሣት (50-58)፡፡