Friday, August 21, 2015

ፍቅር እና ጀበና


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አርብ ነሐሴ 15 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

እዚያ . . . ቡና ጠጡ፤
አሉባልታ አድምጡ።
ብዬ ከወዳጆቼ ተሰባስቤ፤
ለወሬ ተሰናድቶ ቀልቤ።
የሰው ሥጋ ስንቋደስ፤
ስንቀቅል ስንጠብስ።
ከፍም የተገናኘው ሸክላ፤
በእሳቱ ነበልባል ሲበላ።
ድንገት . . . እፍ . . . እፍ . . . ኧረ ገነፈለ፤
ቡናው ከጀበናው ዘለለ።
እኛ ስናወራ እሳቱ አይሎ፤
ጀበናው የውስጡን አወጣ አግተልትሎ፡፡
እዚህ . . . ቡና ጠጡ፤
ቃሉን አድምጡ። 
ብዬ ወዳጆቼን ሰብስቤ፤
ለቃሉ ተሰናድቶ ቀልቤ።
የሰው ነፍስ ስንናጠቅ፤
ከክፉ ሥራ ስናላቅቅ።
ከፍም የተገናኘው ሸክላ፤
በሳቱ ነብልባል ሲበላ።
ድንገት . . . እሰይ . . . እሰይ . . . ገነፈለ፤
ፍቅር ከጀበናው ዘለለ።
ከተሰባሪው ገል ገላ፤
ከእኔነቴ ሸክላ።
የመለኮት እሳት በዝቶ፤
ውስጤን አግሎ አፍልቶ።
እንደ ፈሳሽ ምንጭ፤
ከሰዎች ሲሰራጭ።
የሕይወት ቡና ቢያጠጣ፤
ከሸክላነታቸው ሸክላ ወጣ።
እናንተም የፍቅሩ ቁራሾች፤
የመለኮት እሳት ተካፋዮች።
ከፍቅር ጀበና ገንፍሉ፤
ከሸክላነታችሁ ውጡና ዝለሉ።

                                 ‹‹ . . . ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ፤›› /ቆላ. 4፡3/!
                  

Friday, August 14, 2015

ስፍራችሁን ያዙ

(ካለፈው የቀጠለ)
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

አርብ ነሐሴ 8 ቀን 2007 የምሕረት ዓመት

      ‹‹ነጽር ኀበ አይ መካን አዕረጋ ለቤተ ክርስቲያን ዘከመ ይእቲ ኩለን ሰሐባ በጥበብ እምሉዓሌ፡፡ ወክመዝ አዕረጋ ኀበ ልዕልና ዐቢይ÷ ወለዝንቱ ዘውእቱ እምኔነ አንበሮ ዲበ ዝንቱ መንበር÷ ወለነሂ ዓዲ ለቤተ ክርስቲያን ስሐበነ እግዚአብሔር ኀቤሁ በከዊኖቱ ርእሰ ዚአነ እስመ ውስተ መካን ኀበ ሀሎ ርእሰ ህየ ይሄሉ ሥጋ ቤተ ክርስቲያን አካሉ እንደ መሆንዋ መጠን ወዴት ከፍ ከፍ እንዳደረጋት አስተውል፡፡ ከላይ ሆኖ በጥበብ ወደ እርሱ አቀረባት እንደዚህ ወዳለ ክብርም አወጣት ከእኛ ወገን የሆነውን /ከመለኮት ጋር የተወሐደውን/ ትስብእትንም በዚያ ዙፋን በቀኙ አስቀመጠው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሆንነውን እኛንምርስቶስ ራሳችን በመሆኑ እግዚአብሔር ወደ እርሱ ሳበን÷ ራስ ካለበት ሕዋሳት ይኖራሉና››      

/ሃይማኖተ አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ፤ 67÷39/