Friday, January 13, 2012

ውበት ሲብራራ


ውብ እጆች፡- ላዘኑት ደማቅ የደስታ ክርን በሕይወተታቸው የሚሠሩ በረከቶች ናቸው።
ውብ እግሮች፡- ከጸሐይ መውጫ እስከ ጸሐይ መግቢያ ድረስ ለይቅርታ መልዕክት የሚሮጡ መዳረሻዎች      ናቸው።
ውብ ቅርጾች፡- የተዋረደውን ቦታ ረጋ ካለ አገልግሎት ጋር ሞገስ የሚሰጡ ትሁታን ናቸው።
ውብ ፊቶች፡- መለኮታዊ በሆነ ፍጹም ፍቅር የሚያንጸባርቁ ገጾች ናቸው።
ውብ ከናፍሮች፡- ያዘኑትን የሚያጽናኑ፣ የደከሙትን የሚደግፉ፣ የወደቁትን የሚያነሱ የእውነት ዙፋን ናቸው።
ውብ ዓይኖች፡- እንደ በረዶ በነጣ መንፈስ በጨለማው ላይ የሚያበሩ ከዋክብት ናቸው።
ውብ ነፍሳት፡- በተገኙበት ቦታ ሁሉ የእግዚአብሔርን መፍትሔ የሚያሳዩ ታማኝ ሎሌዎች ናቸው።
ውብ ነዋሪዎች፡- ለሌሎች ኑሮ የሌሎችን ድካም የሚሸከሙ ቅን ትከሻዎች ናቸው።
የእውነተኛ ሰብእና ሕያው ድምቀት፤ አማላይ ውበት ያለው በዚህ ውስጥ ነው፡፡ ለእኛም ሆነ ለሌሎች ሕይወት ትርጉም የሚኖራት መኖርም በናፍቆት የሚቃኘው በዚህ ከተገኘን ብቻ ነው!

2 comments:

  1. ስለ ውበት የነበረኝን አመለካከት አስተካክሎልኛል:: Thank u ..

    ReplyDelete