Tuesday, December 25, 2012

ሥራህን ሥራ!




                                         ማክሰኞ ታህሳስ 16/2005 የምሕረት ዓመት

           ጌታ ለእያንዳንዱ ሰው ሥራ ሰጥቶታል ያንን መሥራት የእርሱ ፈንታ ነው፡፡ ቢቻለው እሱን ማገድ የዲያቢሎስ ሥራ ነው፡፡ በእርግጥ ሥራውን እግዚአብሔር እንደሰጠህ ያህል ሰይጣን ሊያግድህ ይሞክራል ሌላ ነገር በበለጠ ደስ የሚያሰኝ ሊያቀርብልህ ይጥራል፡፡ በዓለማዊ ተስፋዎች ያባብልሃል የሃሜት ጎርፍ ያስወርድብሃል በሐሰተኛ ክስ ያሰቃይሃል ለክብርህ እንድትከላከል ያደርግሃል ደራሲያን እንዲጠይቁህ እጅግ ስመ ጥር ሰዎች በክፉ እንዲናገሩህ ይጠቀምባቸዋል፡፡
           ጲላጦስ፣ ሄሮድስ፣ አናንያ፣ ቀያፋ በአንተ ላይ ያድማሉ ይሁዳም በአጠገብህ ቆሞ በሰላሳ ብር ሊሸጥህ ይከጅላል፡፡ አንተም “ይኸ ሁሉ የመጣብኝ ለምንድን ነው?” በማለት ይደንቅሃል ይኸ ሁሉ የመጣብህ ሰይጣን በዘዴ ከሥራህ ሊስብህና እግዚአብሔርን ከመታዘዝ ሊያሰናክልህ መሆኑን ልትገነዘብ አትችልምን?
           ሥራህን ሥራ አንበሳው ቢያጓራ ፍንክች አትበል፣ የሰይጣንን ውሾች ለመውገር አትቁም፣ ጥንቸሎቹንም  በማባረር ጊዜህን አታጥፋ፣ ሥራህን ሥራ ዋሾቹ ይዋሹ ጠበኞቹ ይጣሉ ማኅበረኞቹ ይወስኑ፣ ደራሲዎቹ ይድረሱ፣ ሰይጣንም የፈለገውን ያድርግ አንተ ግን ምንም ነገር እግዚአብሔር የሰጠህን ሥራ ከመፈፀም እንዳያግድህ ተጠንቀቅ፡፡
           ገንዘብ እንድታተርፍ አልተላክም፣ እንድትበለፅግም አላዘዘህም፣ ሰይጣንና አገልጋዮቹ የሚነዙትን የሐሰት ወሬ እንድታስተባብል አልተጠየክም እነዚህን ሁሉ ነገሮች ብታደርግ ሌላ ሥራ ልትሠራ አትችልም፤ ይህም ብቻ ሳይሆን ለራስህ እንጂ ለጌታ አልሠራህም፡፡
           ሥራህን ሥራ ዓላማህ እንደ ኮከብ የፀና ይሁን፣ ተወው ዓለም እንደፈለገው ይነታረክ ይጨቃጨቅም፡፡ ጥቃት ይደርስብህ፣ ትበደል፣ ትሰደብ፣ ትታማ፣ ትቆስል፣ ትናቅ ይሆናል፡፡ ኃይለኛ ያጎሳቅልህ፣ ወዳጆችህ ይተዉህ፣ ሰዎች ይንቁህ ይሆናል፡፡ አንተ ግን የፀና ውሳኔ በማያወላውል ቅናት በመጨረሻ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈፀምኩ ለማለት እስክትችል ድረስ የሕይወትህን ዓላማና የተፈጠርክበትን ግብ ተከተል፡፡

5 comments:

  1. zat is very intersting issue. but how we know that sth. is my life goal or not? i don't get an answer for this question for years? please say something.....b blessed!

    ReplyDelete
  2. telat kifu biyawera diyabilos yetunim yahil bitir egna gin ke ashenafiw gar nenina lezelalem anwedkim!

    ReplyDelete
  3. yetenesaw hasab bizu negerochin medases silemiyaschil ketay kifil binorew tiru new...Egziabher yibarkachu!

    ReplyDelete
  4. amen yetefeternibetin gib endiniketel Egziabher yirdan!

    ReplyDelete
  5. Thank you for the great encouragment. It was just in time for me. May God continue to bless you and I look forward to read more.
    D.yeneneh

    ReplyDelete