Tuesday, January 15, 2013

የቆቅ ትዳር



                                                                   

                                             ማክሰኞ ጥር 7/2005 የምሕረት ዓመት

         ከወደ አውሮፓ የሰማሁት አንድ ነገር ትዝ ይለኛል፡፡ ልጅቱ እና ልጁ በእጮኝነት የአራት አመታት እድሜ አስቆጥረዋል፡፡ በእነዚህ ጊዜያት ሁሉ በአንድ እጅ የመብላትና በአንድ አፍ የመናገርን ያህል የፍቅር ቅርበትና መዋደድ ነበራቸው፡፡ ታዲያ ለመጋባት ወስነው ቀን ይቆርጣሉ፡፡ በዚያም ቀን የቤተክርስቲያኑ አዳራሽ በታዳሚ ጢም ብሎ ሙሽራውና ሙሽሪት ለቀለበትና ለፊርማ ስነ ሥርዓት ወደተዘጋጀው መድረክና ይህንን ወደሚያስፈጽሙት የሃይማኖት አባት በእርጋታ ይቀርባሉ፡፡ ድንገት ባል ፊርማውን በተዘጋጀው ምስክር ወረቀት ላይ አስፍሮ እንደጨረሰ የሚስቲቱ ተራ ሲደርስ ቬሎዋን ሰብስባ ከፍ ባለ ድምጽ “አንተ አታገባኝም . . . . አዎ! አንተን አላገባም” እያለች ከአይን ያውጣሽ በሚያስብል ድፍረት በእድምተኛው መሐል ተወራጭታ ወጣች፡፡ ግን ምክንያቷ ምን ይመስላችኋል?

         የጥርን ወር መበሰር ተከትሎ አንድ ነገር ያስተዋላችሁ ይመስለኛል፡፡ የጋብቻ ስነ ሥርዓት ! እንደ እግዚአብሔር ሰው በሁለት ሰዎች አንድ ሥጋ መሆን ደስታ ሲሰማን፤ በትዳር ውስጥ ለሚፈጠረው የከፋ ችግር በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የጦሱ ሰለባ መሆናችንን ስናስብ ደግሞ ሥጋትና ሀዘን ይከብበናል፡፡ ውድ የቤተ ፍቅር ብሎግ ተከታታዮች ጋብቻን በተመለከተ ብዙ ችግሮች እንዳሉ ያለ ነጋሪ የምናውቀው ሐቅ ነው፡፡

         የአንድን ወንድና የአንዲትን ሴት ትዳር የተሻለ ውበትና ሰላም የሚሰጥ ጥቂት መፍትሔ በልባችሁ እንዳለ ከተሰማችሁ አልያም በዚህ ርዕስ ዙሪያ እኔ ላካፍል የምችለው አሳብና ገጠመኝ አለኝ የምትሉትን ከታች ባለው አስተያየት መስጫ ውስጥ በመፃፍ እንድትወያዩበትና ቆቅማ የሆነውን ግን ጥበብ የሌለውን የትዳር ኑሮ እንታደግ በማለት እንጋብዛለን፡፡ በሚቀጥለው ጽሑፍ ስንገናኝ ከላይ የጠየቅናችሁን ጥያቄ መልስና ሰፋ ያለ ማብራሪያ ለማቅረብ እንሞክራለን፡፡ በጸሎት አግዙን!

                                                               - ይቀጥላል -  
        

No comments:

Post a Comment