እሮብ ህዳር 15 ቀን 2008 የምሕረት
ዓመት
ሀ ሁ አቡጊዳ ፊደልን ሊቆጥሩ
ከምምሩ የኔታ ፊት ተኮለኮሉ፤
ትንሽ ምላሶች ይንጫጫሉ
ከወረኛ ዓለም እንዲቀላቀሉ፤
እኒያኛው የሥጋ የኔታ
ዘርግተው የፊደል ገበታ፤
ሲያሻቸው ሲተኙ ሲያንቀላፉ
ሲሻቸው ሕጻናት ሲያስለፈልፉ፤
ብላቴኖቹ ፊደል ቆጥረው ሲጨርሱ
የምምሩም እግሮች አብረው ተነሡ፤
. . . ሌላኛው የኔታ የጠልጣላ ነፍሴ
ቢያሳስባቸው መዳን መቀደሴ፤
የተግባር ትምህርት ሲጀምሩ
እጆቻቸው በምስማር ተቸነከሩ፡፡
/ከቤተ ፍቅር ቤተሰብ የተላከ/
‹‹ . . . ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ፤›› /ቆላ. 4፡3/!
‹‹ . . . ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ፤›› /ቆላ. 4፡3/!
No comments:
Post a Comment