Thursday, April 5, 2012

መጽናናት




     በአዲሱ እለት አጥቢያ ላይ ከእንቅልፌ ስነቃ ልክ የመከራ ወጀብ ወደ እኔ እንደሚመጣ መስሎ ተሰማኝ፡፡ ማየት የቻልኩት ሁሉ ከችግር ቀጥሎ የሚመጣ ሌላ ተግባር ነው፡፡ እናም ጮኼ ማልቀስ ጀመርኩ አቤት ጌታዬ ከእኔ የምትፈልገው ምንድን ነው?” ከከፍታው የመጣው ምላሽ ምንም ሳይሆን በጣም ቀላል ምላሽ ነበር፡፡ አንድ ያልተጠበቀ ነገር ግን እውነተኛ ምላሽ፡፡ ከእኔም ሆነ ከእናንተ የሆነ የሚፈልገው ነገር አለ፡፡ ሁሉንም ነገርሲል መለሰልኝ፡፡ እንደ አዳኝህና እንደ መሪህ ሁልጊዜም በመንገድህ ሁሉ አብሬህ እንዳለሁ የአንዲቷ ፀጉርህ ዘለላ እንኳን ወዳጅ፤ እኔ እንደሆንኩ እንድታውቅ እፈልጋለሁ፡፡

     በመልካም ጊዜያትም ሆነ በክፉዎቹ በእውነትና በመንፈስ እንድታገለግለኝ፣ ተደሰትክም ተከፋህም በምስጋና መሥዋዕት እንድታከብረኝ እፈልጋለሁ፡ በእያንዳንዷ እለት እምነትህ እየጠነከረ እንዲያድግ ለምንለሚሉት ጥያቄዎችህ መልስ ባይኖርህም እንኳን በእኔ እንድታምን እፈልጋለሁ፡፡ ያጋጠመህን አስቸጋሪ ነገር እንድትኖርበት ስትጠራ፤ የእኔን ፍቅር እንድትማርና እቅፌም እንዲሰማህ እፈልጋለሁ፡፡ ማንም ሆነ ምንም በልብህ ያለኝን ቦታ እንዲወስድ አልፈልግም፡፡ ልታደርገው በሚገባህ በማንኛውም ነገር ውስጥ ቀዳሚና ትልቅ ድርሻ እንዲኖረኝ እፈልጋለሁ፡፡ ምንም ነገር አያናውጽህ በቃል ኪዳኔም ጽና በስተመጨረሻም ሁሉ ነገር ተከናውኖልህ ታያለህ፡፡ እስኪ አስብ?

W ሕመም የማይሰማህ ቢሆን ፈዋሽ መሆኔን እንዴት ታውቃለህ?

W በመከራ ውስጥ ካላለፍክ ነፃ አውጪ መሆኔን እንዴት ልታውቅ ትችላለህ

W ብስጭት ካልተሰማህ እንዴት ሆሃ ምቹ እንደሆንክ ታውቃለህ

W ፈተናዎች ከሌሉብህ እንዴት አድርገህ ራስህን ጽኑ እኔን አሸናፊ ብለህ ልትጠራ ትችላለህ?

W ስህተቶችን ጭራሽ ካልሠራህ ይቅር ባይ መሆኔን እንዴት ማወቅ ይቻልሃል?

W ሁሉን የምታወቅ ከሆነ ጥያቄዎችህን ሁሉ እንደምመልስልህ በምን ታውቃለህ?

W ጭራሽ ያልተሰበርክ ብትሆን ኖሮ ሙሉ ላደርግህ እንደሚቻለኝ ከወዴት ታውቃለህ?

W የማልቀጣህ ቢሆን እኔ እንደምወድህ፣ አንተም ልጄ እንደሆንክ እንዴት ትረዳለህ?

W ኃይል ሁሉ ቢኖርህ በእኔ ላይ መደገፍን እንዴት ልትማር ትችላለህ?

W ሕይወትህ ፍጹም ቢሆን ኖሮ ከእኔ የምትፈልገው ምን ይኖር ነበር?

        አየህ ውድ ልጄ በሁሉም ነገር ውስጥ ሁሉ ነገርህ እንድሆን እና ወደቅህም ጸናህም በእኔ መኖር ላይ እንድትደገፍ እፈልጋለሁ፡፡ ከእኔ የምትፈልገው ምንድነው? ለሚለው ጥያቄህ መልሴ ሁሉንም ነገርየሚል ነው፡፡ ልክ አንተ ለእኔ ሁሉ ነገር እንደሆንክ ሁሉ፡፡ ከግርግርና ከፈተና የጸዳ ቀለል ያለ ሕይወትን መፈለግ ለብዙዎቻችን አዲስ ነገር አይደለም፡፡ ይልቁንስ የማንረዳው ነገር ቢኖር ያለ ውጣ ውረድ የምንኖርባት ሕይወት ያን ያህል የሻትነውን ነገር ከግቡ ለማድረስ እንደማታስኬደን ነው፡፡

     ደስታን ለማድነቅ ሐዘን ያስፈልጋል በትንሽ ስጦታ ውስጥ እርካታን ለማግኘት መሰላቸት ይኖራል፡፡ ይህም እያንዳንዱን አስፈላጊ ሥራ የምናደርግበትን፣ አዳዲስ አሳቦችን የምናፈልቅበትን እና አስቀድመን የያዝነውን ጸጋ የምንናፍቅበት እድል የሚፈጥርልን ነው፡፡ ቢሆንም ግን ልብ ልንለው የሚገባን ነገር ሕይወት የተመሠረተችው እኛ በከፊል በምናደርገው ነገር ላይ ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ለሰው በሚያደርገው ሙሉ ነገር ላይ መሆኑን ነው፡፡ ሙሉ እኛነታችን ይህንን ታላቅ እውነት እስካልተቀበለውና እስካልኖርንበት ድረስ መልካምነትና ሰላም በሙላት በእኛ ውስጥ ሊኖር አይችልም፡፡ እርሱ ብቻውን እውነተኛ አዳኝ ነው፡፡ ስለዚህ በዋናነት በራሳችን ላይ የምንደገፍ ከሆነ ሕይወት የማይገፋ እየሆነብን ይመጣል፡፡ የእግዚአብሔር ጸጋ ሕልውናችን ነው፡፡ በእርሱ ላይ እንሄዳለን፡፡ እርሱንም እንተነፍሳለን፡፡ በእርሱም ውስጥ ኖረን በእርሱም ውስጥ እንሞታለን፡፡

1 comment: