Friday, April 13, 2012

ታርዶልሃል



ታርዶልሃልና በጉ
ተሰጥቶሃል የመግቢያ ካርዱ
ወደ ትልቅ ግብዣ ወደ ሠርጉ
ቤዛ ከኃጢአት መዋጃ
ምትክ ለበደላችን ካሳ
የተትረፈረፈ መከር
የማይጎድል ጥጋብ
ሆኗልና በጉ
በሐሴት በእልልታ ግባ ወደ ሠርጉ
ሸክም ጭነት ተራግፎልህ
የሞት መውጊያው ተሰብሮልህ
ተዘልለህ እንደ ዘሩባቤል
መኖሪያህ እንዲደላደል
ኪዳንህን አጽና በደሙ
ሞት ተደምስሷል በስሙ፡፡
                              - ካንባቢ -

No comments:

Post a Comment