Saturday, December 17, 2011

ሕይወት ሲካፈል



የምትጋጠመው   -     ግጥሚያ
የምትቀበለው     -     ስጦታ
የምትጋራው      -     ጀብዱ
የምትጋፈጠው   -      መከራ
የምትወጣው     -     ሐዘን
የምትከውነው   -     ግዴታ
የምትጠቀምበት  -     አጋጣሚ
        የምትፈጽማት   -     ጉዞ
        የምትጠብቃት   -     ቃል ኪዳን
        የምታሟላት      -     ጉድለት
የምትንከባከባት   -    ፍቅር
        የምታሳካት       -     ግብ
        የምታወድሳት     -     ውበት
        የምትፈታት       -     እንቆቅልሽ ናት!

ሞት የሚሆነው ለሞቱ ሰዎች ብቻ ነውና በሕይወት ያለ ሰው ሞትን ያስንቃል፡፡  ከሞት በኋላ ሊሆን ለሚችለው ነገር ከሚኖርህ አሳብ በበለጠ ከሞት በፊት ስለሚሆኑት ነገሮችና መሆን ስለሚገባህ አስብ ምክንያቱም ያ ውጤት ነውና፡፡ ከሞት በፊትም ቀድመህ አትሙት፡፡ ኑርልን!
 ሻማ ብርሃኑን ካልሰጠ በቀር ሊያበራ አይችልም፡፡ የሚታየው በራሱ ብርሃን ነውና፡፡ ለሌሎች ብርሃንን በመስጠት ያበራል፡፡ ታዲያ ለምን ብርሃንህ እንዲያበራ አትፈቅድለትም፡፡ ራስህንና የራስህን ለሌሎች አካፍል በቃ! አካፍል አሁንም  አካፍል ደግሞ አሁንም አካፍል . . . ምን እንደሚሆን ታውቃለህ? በረከት ጓዙን ጠቅሎ በአንተ ውስጥ ይከትማል፡፡ አትኩሮት፣ ፍቅርና ደሰታን ስጥ፡፡ በየዕለቱ ስጥ፡፡ ለመስጠት አስቸጋሪ ቢሆንም እንኳን አንተ ግን ስጥ፡፡ ምንም ምላሽ ሳትጠብቅ ስጥ፡፡ መቀበል ብትፈልግ እንኳን ስጥ፡፡ ትልልቅ ዋጋ የሌላቸውን ነገሮች እንኳን ቢሆን ስጥ፡፡ መስጠትህንና ማካፈልህንም አታቋርጥ፡፡

No comments:

Post a Comment