Wednesday, December 21, 2011

ዝም ስል


በገናውን ብደረድር ጸናጽሉን  ብጸነጽል
ከበሮ ብመታ እንቢልታ ብነፋ
ክራርና ዋሽንት የአታሞ ቅኝት
በመዝሙር ብርቱ ቃል ብዘል እንደንቦሳ
አይገልጠውም ውስጤን ሳስብ ውለታህን  
እጄን ከልቤ ጋር
በእልልታ ሕብር በጭብጨባ ዜማ ለአንተ ከማሰማ
እንደ  ሃና ቅድስት እንደ ሰራፕታዋ የጸሎት መበለት
እንደ ዕንባቆም ነቢይ በዝምታ መኃልይ
ሳስበው እረካለሁ ዝም ስል ጌታዬ በሥራህ አርፋለሁ፡፡ 
        (አቤኔዘር)

2 comments: